ደደሆ

ከውክፔዲያ
ደደሆ

ደደሆ (Euclea racemosa) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሁሌ ለም ዛፍ ወይም ቊጥቋጥ አይነት ነው። ብዙ ቅጠላቅጠልና ትንንሽ ቀይ፣ ሐምራዊና ጥቁር ፍሬዎች አሉበት።

አፋርኛና በሶማልኛ የሌላ ዝርያ ዛፍ Salvadora persica «ደደሆ» ይባላል፤ የዚያው ዛፍ ስም በአማርኛ መሮ ነው።

አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በኮረብቶች ወይም በእዳሪ መሬት ተራ ነው።

በምስራቃዊው አፍሪካ ከግብጽ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ፣ እንዲሁም በኮሞሮስ፣ በኦማንና በየመን ይገኛል።

የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ትንንሽ ፈሬዎቹ ሊበሉ ይቻላል፤ በትልቅ መጠን ቢበላ ግን የሆድ ማበጥ ያደርጋል። ፍሬዎቹም በአዕዋፍ ይበላሉ።

ፍሬዎቹም «የደደሆ ኮምጣጤ» ለመሥራት ይጠቀማሉ።

ጥቁር ፍሬዎቹ ደግሞ ሐምራዊ ቀለም ለመሥራት ይጠቀማሉ።[1]

ፍቼ በተደረገ ጥናት ዘንድ፣ የደደሆ ቅጠል ዱቄት ለጥፍ ለኪንታሮት ይለጠፋል። የቅጠሉ ጭማቂም ለኮሶ ትል ወይንም ለአባለዘር በሽታ ይጠጣል። አገዳውም ለጥርስ ሕመም ይኘካል።[2]

  1. ^ አማራ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች