ደጃዝማች ወልደ ሰማዕት

ከውክፔዲያ

ደጃዝማች ወልደ ሰማዕት'ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ወላይታ አውራጃ በአስተዳዳሪነት በቆዩበት ጊዜ ብዙ የልማት ሥራዎችን አከናውነዋል።

ከሠሯቸው አበይት ሥራዎቻቸውም ፦

  • ሰባቱንም ወረዳዎች የሚያገናኝ መንገድ አሰርተዋል።
  • በሚሲዮናዊያን አማካኝነት የመጀመሪያውን የደቡብ ሆስፒታል አስገንብተዋል።
  • ወላይታን ከምዕራብ ኢትዮጵያ የሚያገናኝና ፺ ሜትር ርዝመት ያለውን ታሪካዊውን የኦሞ ድልድይ አሠርተዋል።
  • ወጣቱ ትርፍ ጊዜውን የሚያሳልፈበትን ወ.ወ.ክ.ማ. (የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር የወጣቶች መንደር ከዘመናዊ ቤተ-መጻሕፍት ጋር አሰርተዋል።
  • ሶዶ ከተማ ዘመናዊ የገበያ አዳራሽ ከማሠራታቸው ነው።
  • ይርጋለም ቀጥሎ በደቡብ የመጀመሪያውን ከፍተኛ ፪ኛ ደረጃ ተማሪ ቤት አሠርተዋል።