ጄረሚ ቤንታም

ከውክፔዲያ
ጄረሚ ቤንታም

ጄረሚ ቤንታም (15 የካቲት 1748–6 ሐምሌ 1832) የነበረ እንግሊዛዊ ፈላስፋሕግ ተማሪ፣ እና ማህበረሰብ አዳሽ ነበር። በአሁኑ ዘመን ጠቃሚያዊነት (ዩትልተሪያኒዝም) እና የእንስሳት መብት ጀማሪ ተብሎ ይታወቃል።

ቤንታም የለዘብተኝነት (ሊብራሊዝም) ዋና ተሟጋች እንደሆነ ግንዛቤ አለ። ቤተ እምነትና መንግስት እንዲለያዩም ይደግፍ ነበር። የሴቶች እኩልነት፣ የመፋታት መብት፣ የባርነት መቅረትን፣ የሞት ፍርድ መቅረትን፣ ተጨባጭ የሰውነት ቅጣት መቅረትን፣ የአንድ አይነት ጾታ ግንኙነት ወንጀል መሆን መቆምን፣ ፓንቶኮፖን የሚባለውን የእስር ቤት አይነት ስራን፣ የመናገር ነጻነትን የወልድ ብድርንና ባጠቃላይ መልኩ ዘመናዊ ለዘብተኞች የሚድገፏቸውን አቋሞች ይደግፍ ነበር። ተማሪወቹ፣ ጆን ስቱዋርት ሚል እና ሶሺያሊዝምን የፈለሰፈው ሮበርት ኦወን የለዘብተኝነት ርዕዮተ አለሙን በማስፋፋት ስሙን እንዲገን አስተዋጽዖ አድርገዋል። ቤንታም ለግለሰብና ለኢኮኖሚክ ነጻነት ተሟጋች ነበር።

ባጠቃላይ መልኩ ቤንታም በዘመናዊ አስተያየቶች ላይ በራሱ ስራና በተማሪወቹ (ለምሳሌ ስቱዋርት ሚል እና ሶሺያሊዝምን ፈጣሪው ሮበርት ኦን)ከፍተኛ ተፅዕኖ ያደረገ ሰው ነበር። ስለሆነም በብዙዎች ዘንድ እንደሚታመነው በታሪክ ዋናው የጠቃሚያዊነት ፍልስፍና አራማጅ ይሄው ሰው ነው።