ፍሬው ኃይሉ

ከውክፔዲያ

ፍሬው ኃይሉ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ድምፃዊ፣ የሙዚቃ አቀናባሪ፣ ተዋናይ እና የግጥምና ዜማ ደራሲ ነው።

የህይወት ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ፍሬው ኃይሉ በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. በትግራይ ክ/ሀገር ተንቤን አውራጃ ተወለደ። ቀደም ሲል በድቁና ሲያገለግል የነበረው ፍሬው በ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት ተቀጠረ። ፍሬው በአኮርዲዮን አጨዋወት ቅልጥፍናው የሚደነቅ ከመሆኑም ሌላ የሙዚቃ አቀናባሪ፣ የተዋጣለት ተዋናይ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ ነበር።

የሥራዎች ዝርዝር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ፍሬው ሀይሉ በሕይወት ዘመኑ ከአንድ መቶ በላይ ዜማዎችን ተጫውቷል። ከተጫወታቸው ዜማዎች በተለይ «ዐይን የተፈጠረው»፣ «እሽሩሩ»፣ «ሱቅ በደረቴ» እና «ኑኑዬ ጨቅላዋ» የተሰኙት ዜማዎች ተወዳጅነታቸው ላቅ ያለ ነው። ፍሬው በ፲፱፻፵፱ ዓ.ም. አምስት የሚሆኑ የባህል ዜማዎችን በሸክላ አስቀርፆ ለሕዝብ አቅርቧል።

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]