4 መንቱሆተፕ

ከውክፔዲያ
የ፬ መንቱሆተፕ ስም በጢንዚዛ ዕንቁ ላይ ተጽፎ

4 መንቱሆተፕ ነብታዊሬ ግብጽን ከጤቤስ (11ኛው ሥርወ መንግሥት) የገዛ ፈርዖን ነበረ። የ3 መንቱሆተፕ ልጅና ተከታይ ነበር።

ነብታዊሬ ለረጅም ጊዜ በግብጽ አልነገሠም። በአጭር ዘመኑ ውስጥ አንዳንድ ተጓዥ ወደ ዋዲ ሃማማት ለድንጋይ ልኮ ነበር። የዚህም ሥራ ዓለቃ አመነምሃት ተባለ።

በቅርብ ጊዜ ውስጥ ይህ አመነምሃት እራሱ ፈርዖንና የ12ኛው ሥርወ መንግሥት መስራች ሆነ። ነብታዊሬ ወዴት እንደ ሄደ ወይም እንደ ኖረ እንዳልኖረ አይታወቅም። የመቃብሩ ቦታ ከቶ አይታወቅም።

ቀዳሚው
3 መንቱሆተፕ
ግብፅ ፈርዖን
2002 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
1 አመነምሃት