ሚያዝያ ፬
ሚያዝያ ፬፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፲፬ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፱ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፶፪ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፩ ቀናት ይቀራሉ።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የሶቪዬት ሕብረት የመጀመሪያውን ጠፈርተኛ፣ የ፳፯ ዓመት የአየር ኃይል ዓባሉን ዩሪ ጋጋሪንን በመኖራኩር ተኮሰች። ጋጋሪን ከባቢ አየርን ሰንጥቆ፣ በኅዋ ምድርን ለአንድ ሰዓት ከአርባ ደቂቃ ያህል ከዞረ በኋላ ወደመሬት ተመልሷል።
- ፲፱፻፸፫ ዓ/ም - የአሜሪካ የበረራ እና የጠፈር አስተዳደር ድርጅት (NASA) ‘ስፔስ ሻትል’ በመባል የሚታወቀውን አየር ዠበብ/የጠፈር መንኮራኩር ለመጀመሪያ ጊዜ ወደጠፈር ተኮሰ። ይኽ የመጀመሪያው አየር ዠበበ/መንኮራኩር ‘ኮለምቢያ’ (Columbia) የተባለው ሲሆን ሃያ ሰባት ጊዜ ወደጠፈር ተተኩሶ ከተመለሰ በኋላ ጥር ፳፬ ቀን ፲፱፻፺፭ ዓ/ም ተመልሶ ወደምድር ሲገባ ተቃጥሎ ተሰባበረ።
ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም ለአሥራ ሁለት ዓመታት አገራቸውን በፕሬዚደንትነት የመሩት አሜሪካዊው ፍራንክሊን ዴላኖ ሩዝቬልት በዛሬው ዕለት አለፉ። ሩዝቬልት የአሜሪካ ፴፪ኛው ፕሬዚደንት ነበሩ።
ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |