አባይ ወንዝ (ናይል)
ከውክፔዲያ
አባይ የሁሉም ነው አባይ መነሻው ኢትዩጵያ ይሁን እንጂ የሚያካልለው አገራት ብዙ ነው ስለዚህ አባይን የግሌ ማለት አይቻልም በአሁኑ ወቅትም ኢትዩጵያ የአባይን ውሃ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ አባይ ለሚያቋርጣቸው አገራት እንዲደርስ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገች ትገኛለች። በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2011 የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ፦ ኢትዮጵያ ሌሎቹን የአባይ ተፋሰስ ሃገሮች በማይጎዳ መልክ በአግባቡ የተቀየሰውን "ታላቁ የህዳሴ ግድብ" ተብሎ የተሰየመውን 5250 ሜጋዋት የሚያመነጭ የሃይል ማመንጫ ጣቢያ ግንባታ መጀመሯን በይፋ አስታውቃለች።ይህ ግድብ የሚገነባው በውጭ የሃብታም ሃገሮች የገንዘብ እርዳታ ሳይሆን በራሷ ህዝቦች የገንዘብ መዋጮ መሆኑን በተለያዩ አጋጣሚወች እየተገለፀ ነው።
| አባይ ወንዝ (ናይል) | |
|---|---|
|
|
|
| መነሻ | አፊካ(ጥቁር አባይ ከኢትዮጵያ ይነሳል፣ ነጭ አባይ ደግሞ ከኃይቆች አካባቢዎች (መካከለኛ አፍሪካ) ይነሳል።) |
| መድረሻ | መዲተራኒያን ባህር |
| ተፋሰስ ሀገሮች | ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ፣ ታንዛኒያ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ኢትዮጵያ፣ ግብጽ፣ |
| ርዝመት | 6,650 km (4,132 mi) |
| የምንጭ ከፍታ | 1,134 m (3,721 ft) |
| አማካይ ፍሳሽ መጠን | 2,830 m³/s (99,956 ft³/s) |
| የተፋሰስ አካባቢ ስፋት | 3,400,000 km² (1,312,740 mi²) |
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |