ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ኅዳር 11
- ፲፱፻፲፰ ዓ/ም - በአሜሪካ የ፲፱፻፷፩ ዓ.ም. የፕሬዚደንትነት ምርጫ ተወዳዳሪ እና የሟቹ የፕሬዚደንት ጆን ፊትዝጄራልድ ኬኔዲ ታናሽ ወንድም ሮበርት ፍራንሲስ ኬኔዲ በዚህ ዕለት ተወለዱ።
- ፲፱፻፵ ዓ/ም - የብሪታንያ አልጋ ወራሽ ልዕልት ኤልሳቤጥ (የአሁኗ ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ) በለንደን ዌስትሚኒስተር አቤ ሌፍተናንት (አሁን ልዑል የኤዲንበራ ዱከ) ፊሊፕ ማውንትባተን አገባች።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - የልደታን አየር ዠበብ ማረፊያ የተካው አዲሱ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ(የቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አውሮፕላን ማረፊያ) በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመርቆ ተከፈተ። በዚሁ ዕለት ንጉሠ ነገሥቱ የዓመቱን የፓርላማ ጉባዔ ከፈቱ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በአስተዳደር ጥፋት እና በሙስና ወንጀል ተከሰው በልዩ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የቀረቡትን የቀድሞ ባለ-ሥልጣናት መመርመሪያ እንዲሆን የተዘጋጀው አዲስ ሕግ በነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር ፰ ታውጆ ወጣ። ይህ ድንጋጌ ባ፲፱፻፵፱ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ላይ ተጨማሪ ነው።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - ከወላይታ-ሶዶ ተነስቶ በምዕራብ ወለጋ ዞን ወደምትገኘው በጊ መንገደኞችን የጫነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዲ-ሲ ፫ (Douglas C-47A-30-DL) ለመነሳት ሲያኮበክብ ተከስክሶ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በዚህ አደጋ ሦስቱ አብራሪዎቹ ሕይወታቸው አልፏል።