የካቲት ፲
ከውክፔዲያ
የካቲት ፲፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፷ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፵፭ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻፮ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፭ ቀናት ይቀራሉ።
ማውጫ |
[ለማስተካከል] ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- ፲፯፻፴፮ ዓ/ም - አጼ ኢያሱ ብርሃን ሰገድ ከጳጳሱ አባ ዮሐንስ እና ከ እጨጌ ኤውስጣቴዎስ ጋር ሆነው አንድ የሶርያ ተወላጅ ነጋዴ በሐሰት ጳጳሱ እኔ ነኝ እያለ ብዙ ሰዎችን በማሳሳቱ አስረው ወደአገሩ አባረሩት።
- ፲፯፻፷፪ ዓ/ም - የስኮትላንድ ተወላጁ ሐዋጼ አህጉር (explorer) ጄምስ ብሩስ በዕለተ ሐሙስ ጎንደር ገባ። እዚሁም እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፯፻፷፬ ዓ/ም ድረስ ተቀመጠ።
[ለማስተካከል] ልደት
- ፲፰፻፹፫ ዓ/ም - ታላቁ ደራሲና ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ክቡር ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው በሸዋ ግዛት ተጉለት፣ አዲስጌ ላይ ተወለዱ።
[ለማስተካከል] ዕለተ ሞት
[ለማስተካከል] ዋቢ ምንጮች
- መርስዔ ኀዘን ወልድ ቂርቆስ፤ ዕለታዊ የታሪክ ድርጊት “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው ፓትረያርክ” (፲፱፻፶፩ ዓ/ም)፣
| የኢትዮጵያ ወራት | |
|---|---|
| መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ | |