ግዕዝ

ከውክፔዲያ
(ከግእዝ የተዛወረ)
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኦሪት ዘፍጥረት 29 በግዕዝ መጽሐፍ ቅዱስ

ግዕዝአፍሪካ ቀንድኢትዮጵያና በኤርትራ በጥንት የተመሠረተና ሲያገለግል የቆየ ቋንቋ ነው። በአክሱም መንግሥትና በኢትዮጵያ መንግሥት መደበኛ ቋንቋ ነበር። ዛሬ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥነ-ስርዓት እንዲሁም በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እና በቤተ እስራኤል ሥነ-ስርዓቶች እስከ ዛሬ ድረስ ይሰማል።

ቋንቋው የሴማዊ ቋንቋዎች አባል እየሆነ በደቡብ ሴማዊ ቅርንጫፍ ውስጥ ይከተታል። ደቡብ ሴማዊ በመባሉ ግዕዝ የሣባ ቋንቋ ቅርብ ዘመድ ነው። ግዕዝ የተጻፈው በግዕዝ ፊደል አቡጊዳ ነው። ይህም ፊደል ደግሞ ዛሬ ለአማርኛትግርኛ ለሌሎችም ቋንቋዎች ይጠቀማል። በመላውም የአፍሪቃ አህጉር ውስጥ የመጀመሪያውና ብቸኛ አፍሪቃዊ የራሱን ፊደላት የያዘ ቋንቋ ሲሆን፣ በዓለምም ላይ ዋናና የስልጣኔ አራማጅ ከሚባሉት ቋንቋዎች አንዱ ነው።

በግዕዝ ጽሕፈት 26 ፊደላት ብቻ ይጠቀሙ ነበር፤ እነርሱም፦

ናቸው።

ሊቁ ሪቻርድ ፓንኩርስት እንደሚጽፍ፣ አንድ ተማሪ በመጀመርያው አመት ፊደሉን ከተማረ በኋለ፣ በሚከተለው አመት መጀመሪያይቱ የሐዋርያው የዮሐንስ መልእክትን ከአዲስ ኪዳን በግዕዝ ከትዝታ ለመጻፍ መማር ነበረበት። በሦስተኛው ደረጃ የሐዋርያት ሥራ በአራተኛውም መዝሙረ ዳዊት በግዕዝ ማስታወስ ነበረበት። ይህንን ከጨረሰ ታላቅ ግብዣ ይደረግና ልጁ ጸሐፊ ይሆን ነበር።

ብሪቲሽ ላይብሬሪ (የእንግሊዝ አገር ብሔራዊ በተ መጻሕፍት) ውስጥ 800 የሚያሕሉ የድሮ ግዕዝ ብራናዎች ኣሉ።

በኢ.ኦ.ተ.ቤ. ትምህርቶች ዘንድ፣ ግዕዝ የአዳምና የሕይዋን ቋንቋ ነበር። ፊደሉን የፈጠረው ከማየ አይኅ አስቀድሞ የሴት ልጅ ሄኖስ ነበረ። ከባቢሎን ግንብ ውድቀት በኳላ፣ ከአርፋክስድ ወገን የዮቅጣን ልጆች ቋንቋውን እንደ ጠበቁት ይባላል። የዮቅጣን ልጅ ሣባ ነገዶች ከዚያ ቀይ ባሕርን አሻግረው ወደ ዛሬው ኢትዮጵያ ያስገቡት ይታመናል። እንዲሁም ካዕብ እስከ ሳብዕ (አናባቢዎችን ለመለየት) ወደ ፊደል የተጨመረበት ወቅት በንጉሥ ኤዛና ዘመን እንደ ነበር ይባላል።

ማውጫ

ስዋሰው[ለማስተካከል]

አንድ የግዕዝ ሰነድ ውዳሴ ማርያም (1867 ዓ.ም. ገደማ)

ግሥ[ለማስተካከል]

  • ግዕዝ - አማርኛ
  • ነገረ - ነገረ
  • ነገረት - ነገረች
  • ነገርከ - ነገርክ
  • ነገርኪ - ነገርሽ
  • ነገርኩ - ነገርኩ
  • ነገሩ - ነገሩ
  • ነገራ - እነርሷ ነገሩ
  • ነገርክሙ - ነገራችሁ
  • ነገርክን - እናንቺ ነገራችሁ
  • ነገርነ - ነገርን
  • ይንግር - ይነግራል
  • ትንግር - ትነግራለች
  • ትንግር - ትነግራለህ
  • ትንግሪ - ትነግሪያለሽ
  • እንግር - እነግራለሁ
  • ይንግሩ - ይነግራሉ
  • ይንግራ - እነርሷ ይነግራሉ
  • ትንግሩ - ትነግራላችሁ
  • ትንግራ - እናንቺ ትነግራላችሁ
  • ንንግር - እንነግራለን

ምሳሌ[ለማስተካከል]

«ቃለ፡ በረከት፡ ዘሄኖክ፡ ዘከመ፡ ባረከ፡ ኅሩያነ፡ ወጻድቃነ፡ እለ፡ ሀለው፡ ይኩኑ፡ በዕለተ፡ ምንዳቤ፡ ለአሰስሎ፡ ኲሉ፡ እኩያን፡ ወረሲዓን።» (መጽሐፈ ሄኖክ 1፡1)

ሄኖክ መጀመርያ ቃሎች በጽሕፈት በግዕዝ የጻፈ እንደ ነበር ስለሚባል፣ ይህ ቃል በማንኛውም የሰው ልጅ ቋንቋ ከሁሉ አስቀድሞ የተጻፈ መሆኑ በብዙዎች የኢትዮጵያ ሊቃውንት ይታመናል።

ደግሞ ይዩ[ለማስተካከል]

  • ኣበራ ሞላ - ከቅርብ ጊዜ ወዲህም እዚህ ገጽ ላይ እንደሚታየው ግዕዝን በኮምፕዩተር መጻፍ ተችሏል።

የውጭ መያያዣዎች[ለማስተካከል]