ሆኒያራ

ከውክፔዲያ

ሆኒያራ (Honiara) የሰሎሞን ደሴቶች ዋና ከተማ ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 54,600 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 09°28′ ደቡብ ኬክሮስ እና 159°57′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ሆኒያራ ከ2ኛ ዓለማዊ ጦርነት በኋላ በቀድሞው ዋና ከተማ በቱላጊ ፈንታ ዋና ከተማ እንዲሆን ተሠራ። ዋና ከተማ በኦፊሴል የሆነው በ1944 ነበር።