ሐምሌ ፳፬

ከውክፔዲያ
(ከሐምሌ 24 የተዛወረ)

ሐምሌ ፳፬

ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፳፬ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ዮሐንስ ፵፪ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስማርቆስ እና ሉቃስ ደግሞ ፵፩ ዕለታት ይቀራሉ።

ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፮፻፲፩ ዓ/ም የመጀመሪያዎቹ አፍሪቃውያን ”ተገዳጅ ሎሌዎች” ወይም ባሪያዎች በዩናይትድ ስቴትስ ጄምስ ታውን፣ ቨርጂኒያ የሚባል ሥፍራ ላይ ከመርከብ ወረዱ።

፲፯፻፷፮ ዓ/ም ጦቢዛ[1] (Oxygen) የተባለው “ቶስመክ”[2] (element) ጆሴፍ ፕሪስትሊ በሚባል እንግሊዛዊ ተገኘ።

፲፯፻፺፫ ዓ/ም የታላቋ ብሪታንያን እና የአየርላንድን ንጉዛቶች [3] በማዋሃድ የአሁኗን የታላቋ ብሪታንያና የሰሜን አየርላንድ ንጉዛት ያስፈጠረው ሕግ ጸደቀ።

፲፰፻፳፮ ዓ/ም በጠቅላላው የብሪታንያ ንጉዛቶች “ተገሎሌ"[4] ወይም ባርነትን የሚደመስሰው ሕግ ተደንግጎ ጸደቀ። ሆኖም ሠራተኛ ያልሆኑ ተገሎሌዎች ሕጉ በጸደቀ በአራት ዓመቱ በዚሁ ዕለት በ፲፰፻፴ ዓ/ም ነጻነታቸውን ሲያገኙ ሠራተኛ ተገሎሌዎች ደግሞ ስድስት ዓመት ቆይተው በዚሁ ዕለት በ፲፰፻፴፪ ዓ/ም ነጻ ወጡ።

፲፱፻፶፪ ዓ/ም ዳሆሚ ትባል የነበረችው የአሁኗ ቤኒን ነጻነቷን ከፈረንሳይ ተቀዳጀች።

፲፱፻፶፭ ዓ/ም በኮንጎ ሽብር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታ አስከባሪ ጦር ኃይሎች ጠላይ አዛዥ ሆነው ያገለገሉት ሌተና ጄኔራል ከበደ ገብሬ የሥልጣን ጊዜያቸውን በዚህ ዕለት አጠናቀቁ።[5]

፲፱፻፶፮ ዓ/ም የቀድሞዋ የቤልጅግ ኮንጎ ስሟ ተለውጦ የኮንጎ ሪፑብሊክ ተባለች።


ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ መስፍን አረጋ (ዲባቶ )"ሰገላዊ አማርኛ" ፣ (፳፻ ዓ/ም) ገጽ 90፣
  2. ^ መስፍን አረጋ (ዲባቶ )"ሰገላዊ አማርኛ" ፣ (፳፻ ዓ/ም) ገጽ 41
  3. ^ ንጉሣዊ እና ግዛት የሚሉትን ቃላት በማጣመር kingdom ለሚለው ቃል ፍቺ እንዲሆን የተፈጠረ
  4. ^ ተገዳጅ እና ሎሌ የሚሉትን ቃላት በማጣመር slave ለሚለው ቃል ፍቺ እንዲሆን የተፈጠረ
  5. ^ (እንግሊዝኛ)P.R.O., FCO 371/178551 Annual Review of 1963