ኽያን

ከውክፔዲያ
(ከሕያን የተዛወረ)
ሰኡሰረንሬ ኽያን
የኽያን ካርቱሽ ያለበት ቅርስ
የኽያን ካርቱሽ ያለበት ቅርስ
የግብጽ (ሂክሶስ) ፈርዖን
ግዛት 1638-1602 ዓክልበ. ግ. ?
ቀዳሚ አፐር-አናቲ
ተከታይ ሻሙቄኑ
ሥርወ-መንግሥት 15ኛው ሥርወ መንግሥት


ሰኡሰረንሬ ኽያንጥንታዊ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን15ኛው ሥርወ መንግሥት (ሂክሶስ) ፈርዖን ነበር። ስሙና ሕልውናው ከበርካታ ቅርስ ይታወቃል። ከግብጽ ውጭ ስሙ በክኖሦስቀርጤስ በክደን ላይ ከቤተመንግሥት በታች ተገኘ። እንዲሁም በደቡብ ግብጽ፣ ሐቱሳሽ ሐቲና በባቢሎን አካባቢ በመገኘቱ ንግድ ወደነዚህ አገራት እንደ ላከ ይሆናል። የእርሱ ቤተመንግሥት በቅርቡ በአቫሪስ ተገኝቷል።

ማኔቶን ልማድ እንደ ተገለጸ፣ የሂክሶስ ሦስተኛ ንጉሥ «አፓሕናን» ይባላል፣ ለ36 ወይም በሌላ ቅጂ ለ63 ዓመታት ገዛ። እነዚህ ስሞች በዘመናት ላይ ከግብጽኛቅብጥኛግሪክኛና በሌሎች ልሳናት በኩል በመተረጎማቸው ቢዛቡም፣ ይህ ሦስተኛ ሂክሶስ አለቃ «አፓኽናን» እና «ኽያን» አንድ ሊሆኑ ይቻላል። ስለዚህ በግምት ዘመኑ ምናልባት 1638-1602 ዓክልበ. ያህል ሊገኝ ይቻላል።

በዮሴፉስ ቅጂ ከአፓኽናንና ከአፖፒስ በኋላ «ያናስ» የተባለ ሂክሶስ ፈርዖን ይዘረዘራል። በሥነ ቅርስ ደግሞ በአንዱ ጽላት የኽያን ልጅ ያናሢ ይጠቀሳል። ይህ ያናሢ ምናልባት አልጋ ወራሽ ቢሆንም እንደ ፈርዖን እንደ ገዛ ግን አይመስልም።


ቀዳሚው
አፐር-አናቲ
ግብፅ (ሂክሶስ) ፈርዖን
1638-1602 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ሻሙቄኑ

ዋቢ ምንጭ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]