ሶረን ኬርከጋርድ

ከውክፔዲያ
ሶረን ኬርከጋርድ

ሶረን ኬርከጋርድ(5 ግንቦት, 181311 ህዳር, 1855) የነበረ ዴንማርካዊ ፈላስፋ እና ሥነ መለኮት ተማሪ ነበር። በብዙወች ዘንድ የመጀመሪያው የኅልውነት ፍልስፍና አፍላቂ ተደርጎ ይወሰዳል።

ኬርከጋር ብዙ ስለ እመንትኅልውነትስሜት የሚያትቱ የፍልስፍና መጻሕፍትን ጽፏል። ኬርከጋር ክርስትናን ፖለቲካዊ አቋም እንዲይዝ የሚተጉትን አጥብቆ ተቃውሟል፣ የግለሰብን ነጻነት በቡድን ነጻነት ለመወሰን የሚጥሩንም እንዲሁ ይቃወም ነበር፡፡ ስራው በብዙወች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈለት ሲሆን ሉድቂግ ዋይንሳታይን የተሰኘው የሃያኛው ክፍለ ዘመን ፈላስፋ "ካይከጋርድ" የአ19ኛው ክፍለ ዘመን ስር ነቀል አሳቢ እንደነበር ይገልጸዋል።

የህይወት ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኬርከጋርድ ኮፐንሃገንዴንማርክ ሲወለድ፣ በኮፐንሃገን ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ተከታትሎ በ1841 ዲግሪውን አግኝቷል። ከሴት ጓደኛው ጋር ከተለያየ በኋላ ብዙ መጻህፍትን ሲደርስ፣ እኒህ መጽሃፎች በዘመኑ ያልተወደዱ በ20ኛውና በ21ኛው ክፍለ ዘመን ግን ተደናቂነትን ያገኙ ናቸው።