ቅምቦ

ከውክፔዲያ
ቅምቦ

ቅምቦ ወይም ጦቢያ (Calotropis procera) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቊጥቋጦ ወይም አነስተኛ ዛፍ፣ ወፍራም ልጥ፣ ታላቅ ቅጠል አለው።

አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በቆላ ከ1500m በታች ተራ ነው። በዚህም ውስጥ ደረቅ፣ አሸዋማ ፈሳሽ መውረጃ ይመርጣል።

የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ላስቲኩ ባጠቃላይ ለሰውም ሆነ ለከብት እንደ መርዝ ይቆጠራል። እንስሶች አይበሉትም። ሆኖም፣ ቅጠሉና ቅርንጫፎቹ በመሬት ላይ ለአንድ ሌሊት ቢደረቁ፣ ለከብት መኖ ጸጥ ይላል።

ላስቲኩ የልብ ሽባነት ያደርጋል። እንድ መድሃኒት ለቁምጥና ተጠቅሟል።

አረንጓዴ ቅጠሉ በአፍአዊ አምቅ ማበጥን ለመቀነስ ተጠቅሟል። ሥሩም እንደ ቶኒክ፣ ለአባላዘር በሽቶች[1] ወይም ለእባብ ነከስ[2] እንደሚረዳ ተብሏል።

  1. ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ እስክዳር አበበ - የደባርቅ ባህላዊ ሕክምና 2003 ዓም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ