በልግራድ

ከውክፔዲያ
በልግራድ
በልግራድ

በልግራድ (Београд) የሰርቢያ ዋና ከተማ ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 1.63 ሚሊዮን ሰዎች ሆኖ ይገመታል። ከተማው 44°50′ ሰሜን ኬክሮስ እና 20°30′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ሥፍራው መጀመርያው የተሠፈረው 280 ዓክልበ. አካባቢ በኬልቲክ ነገድ ስኮርዲስኪ ሲሆን ስሙ ሲንጊዱን ተባለ። ወደ ሮሜ መንግሥት በተጨመረበት ወቅት ስሙም በርማይስጥ ሲንጊዱኑም ሆነ። ስሙ በልግራድ (ማለት «ነጭ ከተማ») መጀመርያ የተመዘገበ በ870 ዓ.ም. ጀምሮ ነው።