ብርጭቆ

ከውክፔዲያ
የፊንቄ ብርጭቆ ጋን፣ 1000 ዓክልበ. ግድም

ብርጭቆ ለመቅረጽ የሚችል፣ ብዙ ጊዜ ግልጽ የሆነ ውኁድ ሲሆን ብዙ ጥቅሞች አገኝቶዋል፤ ለምሳሌ መስኮት በመሥራት ይጠቀማል።

ብርጭቆ መጀመርያው በጥንት የተገኘው የሸምበቆ አመድ (አልካሊ) ከቀለጠ አሸዋ (ሲሊካ) ጋራ ሲቀላቀል ነበር። የብርጭቆ ኢንዱስትሪ የጀመረው ምናልባት 1900 ዓክልበ. በፊንቄ ሲሆን፣ ከዚያ አስቀድሞ በተመሳሳይ ዘዴ ሴራሚክ ወይም ሸካክላ በመሥራት በድንገት የተፈጠረ የብርጭቆ ዶቃ አለ።

«ልማዱ፣ ነጥሮንን [እንደ ልብስ ሳሙና የጠቀመ ሶዲየም ከሰላ ወይም አምቦ አመድ] የሸከመ አንድ የንግድ መርከብ በዚህ ቦታ (በቤሎስ ወንዝ አፍ ፊንቄ) እየቆመ፣ ነጋዴዎቹም በዳር ላይ መብላቸውን እያዘጋጁ፣ ድስታቸውንም ለማቆም ድንጊያ ባለመኖራቸው፣ ከመርከቡ የነጥሮን አሞሌ ተጠቀሙ፤ ይህም ከዳሩ አሸዋ ጋር ተባብሮ ሲቀላቀል፣ አዲስ ግልጽ የሆነ ፈሳሽ ፈሰሰ፤ የብርጭቆም መነሻ እንዲህ ነበረ።»[1]
  1. ^ ትልቁ ፕሊኒ XXXVI : 65