ሳሙና

ከውክፔዲያ
ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ሳሙናዎች

ሳሙናጥንተ ንጥር ጥናት ረገድ ከስብ አሲድና ከአልካሊ የተገኘ ጨው ነው። ለማጽዳት እጅግ ጠቀሜታ ያለበት ውኁድ ነው።

በልማዱ ዘንድ፣ ሳሙና መጀመርያ በጥንት የተገኘው እንስሳን በመሠዋት ጊዜ ሞራ ከዕንጨቱ አመድ ጋር በድንገት ሲቀላቀል ነበር። እንዲሁም ነጥሮን (ሶዲየም ከሰላ ወይም አምቦ አመድ) ከዘይት (ለምሳሌ የብርጕድ፣ የሰሊጥ፣ የሰኖባር ወይም የወይራ ዘይት) ጋር በማቀላቀል የልብስ መንፅህ ሥራ ተገኘ።

እነዚህ ጥንታዊ ሳሙናዎች በተለይ ጨርቅን ለማጽዳት ሲሆኑ፣ በ70 ዓ.ም. ግድም ፕሊኒ እንደ ጻፉ የጋሊያ (አሁን ፈረንሳይ) ሕዝብ ሳሙናን ወደ ፀጉራቸው ይጨምሩ ነበር። ከዚያም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለሰውነት ተስማሚ የሆነው ሳሙና ጥቅም ደግሞ ይስፋፋ ጀመር።