ቭየንትዬን

ከውክፔዲያ

ቭየንትዬንላዎስ ዋና ከተማ ነው።

የነጻነት ትግልን ለማስታወስ የተሰራ ሀውልት

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር (1997 ዓም.) 200,000 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 17°59′ ሰሜን ኬክሮስ እና 102°38′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ላዎስ አፈ ታሪክ ጵራ ላክ ጵራ ላም ዘንድ፣ መስፍን ጣታራድጣ ከአፈታሪካዊ ላዎስ መንግሥት 'ምዎንግ ኢንጣፓጣ ማሃ ናኾኔ' በሸሸ ጊዜ፣ ሰባት ራስ ባለበት ዘንዶ ትዕዛዝ ከተማውን 'ቻንጣቡሊ ሲ ሳታናኻናሁድ' ብሎት መሠረተው።

ይሁንና የታሪክ ሊቃውንት እንደሚሉት ግን የቀድሞ ኽመር መንደር መሆኑ ይታመናል። በ1100 ዓ.ም. ያሕል፣ የላውና የጣይ ሕዝቦች አገሩን ከቻይና ወርረው በዚያ አካባቢ የተረፉት ሕመሮች አሳለቁ። በ1552 ዓ.ም. የላን ሻንግ ንጉሥ ሠጣጢራጥ ብይፋ ዋና ከተማ አደረጉት። በ1699 ዓ.ም. የላን ሻንግ መንግሥት ሲወድቅ የራሱ ከተማ-አገር ሆነ። በ1772 ዓ.ም. ተሸንፎ ለጣይላንድ ግዛት ተጨመረ። በ1885 ዓ.ም. ለፈረንሳይ ግዛት አለፈ። የፈረንሳይ ቅኝ አገሩ መቀመጫ በ1891 ዓ.ም. ሆነ።