Jump to content

አሸንዳ

ከውክፔዲያ

አሸንዳ፡ ወይም 'የሴቶች ቀን' የትግራይ ena Amhara ብሄራዊ ባህል ሲሆን በአንዳንድ በትግራይ ena Amhara አዋሳኝ ክልሎች ይከበራል ከዚህም ውስጥ በላሊበላ አገው አከለ ጉዛይ አካባቢዋች ሚከበር ባህል ነው። 300 ዓ.ዓ በሳባውያን ህዝብ በአክሱም ውስጥ እንደተጀመረ የታሪክ አጥኝዋች ይናገራሉ። በዓሉ በወጣት ልጃገረድ ሴቶች በትግራይ ከሚከበሩ ታላቅ በአል አንዱም ነው፣ የትግራይ ሴቶች ይህን በአል ለማክበር በጉጉት ይጠብቃሉ። አሸንዳ ቃሉ ትግርኛ ሲሆን ትርጉሙም ከሳር ዓይነት የተሰጠ ነው፣ አንድ ነጭ ሽንኩርት ቅጠል እሚመስል ሰፊ እና እረዥም ተክል ነው። ይህ ተክል አሸንዳ ተብሎ ለሚታዎቀው በዓል መነሻ ሥምም ነው።

አሸንዳ፣ ከነሐሴ 16 እስከ ነሐሴ 18 ቀን ድረስ በትግራይ ይከበራል በአሉ በቅርብ ጊዜያትም ተወዳጅነቱ በመጨመሩ በኤርትራ፣ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ሸዋ፣ ኦሮሚያ እናም ሌሎች አካባቢዎች መከበር ጀምሯል።