አባ ጉባ

ከውክፔዲያ
አቡነ አባ ጉባ
ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ ናቸው::
የጻድቁን ስዕል ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ
ጻድቅ ፣ ቅዱስ
የተወለዱት ታህሣሥ ፳፱ ቀን ፫፻፴፮ ዓ.ም.
የአባት ስም ጌርሎስ
የእናት ስም ቴዎዶክሲያ
የሚከበሩት በመላው የኢትዮጵያ ርትዕት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተለይ በአድዋ
በዓለ ንግሥ ባረፉበት ዕለት ፣ ግንቦት ፳፱ ቀን በኢትዮጵያ
በየወራቱ የሚታሰቡት ወር በገባ በ፪ኛው ቀን
የትውልድ ሀገር ኪልቂያ


አባ ጉባ የተወለዱት ታኅሣሥ ፳፱ ቀን በ፫፻፴፮ ዓ.ም በመንፈቀ ሌሊት ነው ። አባታቸው ጌርሎስ እናታቸው ቴዎዶክስያ ደጋጎች ሰዎች ነበሩ ። ጉባ ማለትም አፈ መዐር ፣ ጥዑመ ልሳን ማለት ነው ። ከዘጠኙ ቅዱሳንም አንዱ ናቸው ።

አባ ጉባ በተወለዱ ቀን ጌታችን ከመላእክቱ ጋር በመውረዱ ቤታቸው ለሰባት ቀናት በብርሃን ተሞልቶ ነበር ። ሕፃኑ ጉባም ፈጣሪያቸውን "ሃሌ ሉያ" ብለው አመስግነዋል ።

በልጅነታቸው መጻሕፍትን አጥንተው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ገብተው መንነዋል ። ለበርካታ ዓመታት ከተጋደሉ በኋላ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል "ወደ ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያ ሒድ ።" ብሏቸው ከስምንቱ ቅዱሳን ጋር ወደ ሃገራችን መጥተዋል ። ጻድቁ አቡነ አባ ጉባ በአራተኛ አጋማሽ ክፍለዘመን ከዘጠኙ ቅዱሳን ጋር ወደ ኢትዮጵያ ከገቡት ውስጥ አንዱ ናቸው ።

አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞየሕይወት ታሪክ መጽሐፍ የተገኘ በ፲፯ኛው ክፍለ ዘመን የተሳለ የዘጠኙ የቅዱሳኑ ምስል

ጻድቁ አባ ጉባ እንደመሰሎቻቸው በስብከተ ወንጌል ፣ መጻሕፍትን በመተርጐም ፣ ገዳማትን በማስፋፋትና አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽ ቆይተዋል ። በተለይ ራማ ኪዳነ ምሕረት እርሳቸው የመሠረቷት ገዳም ናት ።

ጻድቁ ቅዳሴ ሲቀድሱ ከመሬት ከፍ ይሉ ነበር ። ብዙ ጠበሎችን አፍልቀው ድውያንን ፈውሰዋል። ሙታንንም አንስተዋል ። እመቤታችንም የብርሃን መስቀል ሰጥታቸዋለች ። ጻድቁ ከበርካታ የቅድስና ዘመናት በኋላ በዚህች ቀን ዐርፈው በገዳማቸው ተቀብረዋል ።

በዘመኑ ትኩረ ካጡት ታላላቅ ገዳማት አንዱ ይሄው ትግራይ ውስጥ የሚገኘው የአባ ጉባ ገዳም ነው ።