አንካራ

ከውክፔዲያ

አንካራቱርክ ዋና ከተማ ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 3,582,000 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 3,456,100 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 39°55′ ሰሜን ኬክሮስ እና 32°50′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ኬጢያውያን መንግሥት ዘመን (ከ1200 አክልበ አስቀድሞ) ሥፍራው አንኩዋሽ ተባለ። በግሪኮች ዘመን ይህ አንኩራ (Áγκυρα) ሆነ። በጥቅምት 3 ቀን 1916 ዓ.ም. አንካራ የቱርክ ዋና ከተማ ሆነ።