ኤድስ

ከውክፔዲያ
ኤችአይቪ ኤድስ በአፍሪቃ

ኤድስ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኤድስ አኳየርድ ኢምዩኖደፊሸንሲ ሲንድረም የኤችአይቪየመጨረሻ ደረጃ ነው። ኤችአይቪ ያለበት ሰው ኤድስ ደረጃ ላይ ለመድረስ ብዙ አመታት እንደሚወስድ ጥናት ታረጋግጣል። ኤድስ በኤችአይቪ ሳቢያ የሚመፈጠረው የሰውንት የመከላከያ መዳከም ሲሆን ለተለያዩ በሽታዎች የሚያጋልጥ ደረጃ ነው። አንድ ሰው በኤድስ ሞተ የሚባለው አባባል የተሳሳተ ሆኖ ሳለ በተለያዩ በሽታዎች ተጠቅቶ ነው ወደ ሞት ደረጃ ላይ አንድ ሰው ሊደርስ የሚቻለው። እንዲሁም ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች የፀረ-ኤችአይቪ መዳኒቶችን ሳይጅምሩ የኤድስ ደረጃ ሳይ ሳይርስ ብዙ አመት ሊኖሩ ይችላል። አንድ ሰው የኤድስ ደረጃ ላይ ደረሰ ማለት የሚቻለው የኤችአይቪ ቫይርስ የበሽታ መከላከያ ሃይል ተቁዋማትን ደምስሶ እና ሰውነታችን ከማንኛውም በሽታ የመቁዋቁዋሚያ ሃይሉን በማሳጣት ለተለያዩ ኢንፈክሽኖች ይጋለጣል። የሲዲፎር በመባል የሚታውቀውን በነጭ ደም ሴል ውስጥ የሚገኘውን የሴል ቁጥር (cd4 count) ከ200 በታች በማድረስ የቫይረሱ መጠን በደም ውስጥ እንዲጨምር በማድረግ ለሕይወት ኣደገኛ እና ምቹ ግዝ ተባቂ በመባል የሚታውቁትን በሸታዎች ኦፓርቸንሰቲክ እንፈክሽስ (Opportunistic infections) OIs. በመፍጠር የኤድስ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ያደርጋል። አንድ ሰው አንድ ወይም ሁለት ኢንፌክሽኖች ሲኖሩበት እና በጣም ዝቅያለ የሲዲፎር ሴል ቁጥር 350 cells/mm3 ወይም በታች ሲሆን እና የቫይረሱ ብዛት (viral load) ከ 1,000 copies/mL በላይ ከሆነ የኤድስ ደረጃ ላይ ደረሰ ሊባል ይችላል።

ኤችአይቪ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የበለጠ መረጃ ለማግኘት ዋና ግጽ ላይ ይመልከቱኤችአይቪ

ኤችአይቪ ህዩመን ኢምዩኖደፊሸንሲ ቫይረስ Human Immunodeficiency Virus (HIV) በመባል የሚታውቅ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ቫይረስ የሰውነትን የበሽታ መከላከያ በተለይ የነጭ ደም ሴሎችን በማጥቃት በቀላሉ ሰውነት ለበሽታ እንዲጋለጥ የሚያረግ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ያለባቸው ሰዎች የበሽታው ምልክት ስይታይባቸው ለብዙ አመታት መኖር ይችላሉ። ቫይረሱ በሰውነታ ውስጥ እስከ አስር ዓመት በመቆየት ምንም ሳይታውቅ እና ምንም አይነት ይህመም ምልክት ሳይታይበት በመኖር እና አለማውቅ ከአንድ ሰው ወደሌላ ሰው ሊተላለፍ የሚችል አደገኛ ቫይረስ ነው።

ኤድስ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ የኤድስ ታማሚዎች መኖራችው የተረጋገጠው በ1978 ዓ/ም ነው። በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ 1.3 ሚሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤችአይቪ ቫይርስ ጋር አብረው ይኖራሉ። ኤችአይቪ የሚያመለክት የደም ናሙና የተገኘው በሁለት የደም ናሙናዎችይ ላይ ብቻ ነበር። እነዚህም ከታህሳስ 1976 ዓ.ም እስከ 1977 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከተሰበሰቡ የደም ናሙና የተገኘ በመሆኑ ኤችአይቪ ኢትዬጵያ ውስጥ የተገኘው 1976 ዓ.ም ነው።

ምርመራ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከአካል የሚወጡ ፈሳሾች ላይ ሁሉ ኤችአይቪን ማግኝት የሚቻል ቢሆንም መደበኛ ኤችአይቪ ምርመራ በደም ናሙና ላይ የሚደረግ የኤችአይቪ-1/2 አንቲ ባዲ ምርመራ ነው።

እስታሁን የተሰሩትን የአንቲባዲ ምርመራ አይነቶችን በሁለት ከፍል ማየት ይቻላል።

ኤላይዛ መሰረት አርገው የሚከናወኑ

ኤላይዛ አይ.ኤፍ.ኤ ኤላይዛ-ዌስተርን ብሎት

ፈጣን የኤችአይቪ ምርመራ ማለት ለቫይረሱ የተዘጋጀ አንቲ ቦዲ በደም ውስጥ መኖሩንና አለመኖሩን የሚያመልክት የምርመራ አይነት ነው። በፈጣን የምርመራ ዘዴ ውጤቱን ከ10-60 ደቂቃዎች ውስጥ ማውቅ የሚያስችል የመመርመሪያ ዘዴ ነው።

ምልክቶች HIV

አግልሎ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በኢትዮጵያ ውስጥ በአሁን ሰዓት የኤችእይቪ/ኤድስ ትምህርት በመስፋፋቱ ጥሩ የሆነ ለውጦች በማየት ላይ እንገኛለን። ከቫይረሱ ጋር ለሚኖሩም ሆነ ቫይረሱ እንደሌለባቸው የሚያቁም ሆን የማያቁም የቫይረሱ መስፋፋት ለመግታት የማያቋርጥ ትምህርት ያስፈልጋል። አንድ ሰው ስለኤችእይቪ/ኤድስ ዐውቀቱ ካለው አንደኛ ቫይረሱ እንዳይስፋፋ ይረዳል ሁለተኛ ሰዎችን ከመገለልም ሆነ ከማግለል የሚመጣውን ትልቅ ጥፋት ለመታገል ይረዳል። ከቫይረሱ የበለጠ ሕብረተሰባችን ጎድቶ የነበረ እና አሁንም በመጉዳት ላይ ያለው ይህ አግሎ ነው። እያንዳዱ ገለሰብ ስለኤችእይቪ/ኤድስ ያለው እውቀት ከፍተኛ ከሆነ ከመግላል እና ከመገለል የሚመጣውን መሽማቀቅ እና ጭንቀት መቆጣጠር ከቻልን ማለት ተልቅ ለውጥ እናመጣለን ማለት ነው። ሕብረተሰባችንም ቢሆን ከቫይርሱ ጋር የሚኖሩትን ሰዎች ማግለል እንደሎለብን መረዳት ይኖርበታል። ይሄን ስንል ማግለል የለብንም ብሎ መስበክ ወይም መናገር ብቻ ሳይሆን በዕለት ዕለት ኑሮአችን ላይ በተግባር ማዋል እንዳለብን መረዳት በጣም ጠቃሚ ነው። ይህ የሰውን የማግለል ባህሪ እኛን የአበሻን የጎዳና በመጉዳት ላይ ያለ ስለሆንም ይህ ጎጂ-ባሕል ማስወገድ አለብን። በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ይኸንን ዝምታ የሰበሩ ልንረሳቸው እና ሁሌ ልናስትውሳቸው የሚገቡ እራሳቸውን አውጥተው ከቫይረሱ ጋር እንድሚኖሩ ያስተማሩ እና የብዙ ወጣቶችን ሕይወት ያተረፍ የመጀመሪያው የተስፋ ጎህ ኢትዮጵያማህበር መስራቾች ናቸው።

የኤድስ አመጣጥ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኤድስ በሽታ እንደጀመረ በታማሚዎች ላይ ይታዩ የነበሩት የበሽታ ምልክቶችን በማየት የሰውነት የበሽታ መከላከያ አቅም ከመዳከም ጋር ተያያይዘው የሚመጡ ምልክቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ከመገመት በስተቀር ብዙም የሚታውቅ ነገር አልነበረ፤። ከምን እንደመጣና በምን እንደሚተላለፍ አይታወቅም ነበር። በኋላም በተለያዪ የምርምሮች ዘርፎች ተጠናክረው በመቀጠላቸው የኤድስ በሽታን የሚያመጣው ቫይረስ ለይቶ በማወቅ ተሕዋሱንም በላቦራቶሪ ለይቶ ማውጣት ተችሏል። ይህ የኤድስ በሽታ መንስዔ ተዋሕሳትም በኋላ ላይ ኤችአይቪ የሚለውን ስያሜ አግኝቶዋል ሪትሮ ቫይረስ ከሚባል ተሕዋስ ምድብ ወስጥ መሆኑ ተረጋግጥዋል።

ኤድስ ወይም Acquired Immune Deficiency Syndrome (AIDS) በመባል የታወቀው በሽታ የሚመጣው ህዩመን ኢምዩኖደፊሸንሲ ቫይረስ Human Immunodeficiency Virus (ኤችአይቪ HIV) በሚባል ጀርም ነው። በሽታው የሰውነትን የበሽታ መከላከያ በተለይ ነጭ ሴሎችን በማጥፋት ለቀላል በሽታዎች ለሕይወት ኣስጊ የመሆን ዕድል በመስጠት የሚገድል ነው። የሚተላለፈው ቫይረሱ ያለበት ሰው የተጠቀመበትን ያልፀዳ መርፌ በመጠቀም ወይም ኣስፈላጊዎቹ ጥንቃቄዎች ሳይደረጉ በሚፈጸሙ የተለያዩ የግብረ ሥጋ ግንኙነቶች ነው። ኤድስን የሚያመጣው ሕይወት ያለው ጥገኛ ጠንቅ በኃይለኛ የማጉሊያ መሣሪያዎች ይታያል። ቫይረሱ ሰውነት ውስጥ እያለ እስከ ፰ ዓመታት የማይታመሙና በሽታውን የሚያስተላልፉ ጤነኛ ሰዎች ኣሉ።

የኤድስ በሽታ ሲጀምር ሰውነት ወይም ኣካላችን በቀላሉ የሚከላከላቸው ጀርሞች እንደፈለጋቸው በመባዛት ለሕይወት ኣደገኛ ሆነው ይገኛሉ። ለምሳሌ ያህል ጤነኛ መድን በነበረን ጊዜ ከማይተናኮሉን ባክቴሪያዎች ኣንዱ ኒሞንያ ያስከትላል። የቆዳ ካንሰር (Kaposi's Sarcoma) እና የኣንጎል በሽታም ሊኖሩ ይችላሉ። AIDS-related complex (ARC) ወይም ኣርክ የሚባሉ ምልክቶችም ሊመጡ ይችላሉ። ከእነዚህም መካከል የንፍፊት ማበጥ፣ የማይለቁ ትኩሳቶች፣ ድካምና ተቅማጥ፣ ክብደት መቀንስ (ከ፲ በ፻ በላይ)፣ ደረቅ ሳልና ከባድ የእንቅልፍ ላብ ይገኙበታል። ትረሽ (Thrush) እና ሽንግልስ (Shingles) የሚባሉ በሽታዎችም ሊኖሩ ይችላሉ።

ኤድስ እንዳይዝ የምንከላከልበት የክትባት ዘዴ የለም። በሽታው ከያዘም በኋላ የሚፈውስ መድኃኒት የለም። በኣሁኑ ጊዜ ያለን መከላከያ በበሽታው እንዳንያዝ ኣስፈላጊዎቹን ጥንቃቄዎች ማድረግ ብቻ ነው። በሽታው እንዴት እንደሚተላለፍ በምርምር የተደገፉ መረጃዎችን በመከታተል ተረድቶ ቫይረሶቹ እንዳይሰራጩ ትክክለኛዎቹን ጥንቃቄዎች መከተልና ለሌሎችም ማስተማር የያንዳንዳችን ኃላፊነት መሆን ይገባል። ኤድስ ኣሰቃቂና ኣደገኛ በሽታ ቢሆንም እንደጉንፋን በቀላሉ የሚተላለፍ ስላልሆነ ልንከላከለው የምንችለው በሽታ ነው። ስለ በሽታው በሰፊው ማወቅ ባንፈልግ እንኳን በበሽታው እንዳንያዝ እንዴት እንደምንከላከል መረዳትና ወደ ሌሎች እንዳይተላለፍ እንዴት እንደምንጠነቀቅ ማወቅ እንደሚጠቅሙ ተረጋግጧል።

ኤድስ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው ከ1970 ዓ.ም. ወዲህ ሲሆን እስከ 1985 እ.ኤ.አ. ድረስ የተበከለ ደም በመወጋትና በመሳሰሉት ብዙ ሰዎች ያለቅብጠታቸው በበሽታው ተይዘዋል። ከ1988 ወዲህ ግን ኤድስ ሲይዝ ነጭ ሴል የሚሠራውን ኣንቲቦዲ (Antibody) በመመርመር የኤድስ ቫይረስ እንዳጋጠመን የሚጣራበት ፈጣን የምርመራ ዘዴ ስለተሠራ በተለይ የደም ማነስን ለመከላከል ሆስፒታል ከሚሰጠን ደም በመተላለፍ ሊይዝ የሚችለው ኤድስ ወደ መጣፋቱ ደርሷል።

መተላለፊያው[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኤድስ በሚከተሉት ሁኔታዎች ሊተላለፍ ይችላል።

  • ቫይረሱ ያለበት ሰው የተጠቀመበትን የድረግ (Drugs) መርፌ ሌላ ሰው ቢጠቀምበት (Intravenous) በቫይረሱ መተላለፍ የተነሳ በበሽታው መያዝ ይቻል ይሆናል።
  • በበሽታው ከተያዘ ወይም ቫይረሱ ካለበት ማንኛውም ሰው (ወንድ ወይም ሴት) ጋር የግብረ ሰዶም ግንኙነት (Homosexual, bisexual intercourse) በማድረግ በሽታው ሊይዝ ይችላል።
  • ኤድስ ቫይረሱ ወይም በሽታው ካለበት ሰው ጋር በሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት (Heterosexual intercourse) የሚይዝ የኣባለ ዘር በሽታ ሆኗል።
  • ቫይረሱ ያለባት እናት በሽታውን (ማህፀን ውስጥና በምትወልድበት ጊዜም) ለሕፃንዋ ማስተላለፍ (Intrauterine, perinatal) ትችላለች።
  • በበሽታው የተያዘች እመጫትን የጡት ወተት በመጥባት (በመጠጣት) ሕፃናትን በሽታው ሊይዛቸው (Oral) ይችላል።

መከላከያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከኤድስ በሽታ ለመከላከል የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ይጠቅማል።

  • ከማንኛውም ዓይነት የግብረ ሥጋ ግንኙነት (ከተቻለ) መቆጠብ፣ ወይም ኣንድ ታማኝ የፍቅር ጓደኛ ሌላ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ኣለማድረግ።
  • ለረዥም ጊዜ ተማምነው ኣብረው የቆዩ ባልና ሚስት መስጋትና ለኤድስ ሲባል በኮንዶም (Condom) መጠቀም የለባቸውም። ታማኝነት ከመቼውም ጊዜ ኣሁን ኣስፈላጊ ነው።
  • የሚወጉ ድራጎች (እተደበቁ ተሰባስበው ባልፀዱ መሣሪያዎች ከሚወስዱ ጋር) ኣለመውሰድ። በሽታው ከያዘው ሰው ጋር መርፌና ሲሪንጋ ኣለመጋራት።
  • ከማያውቁት ሰው ወይም ከብዙ ሰዎች ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት በማድረግ ከቆዩ (ኣመንዝራ) ጋር ማንኛውንም ዓይነት የግብረ ሥጋ ግንኙነት ኣለማድረግ።
  • ቫይረሱ እንዳሌለበት ከማያውቁት (ወይም በሽታው ከያዘው) ሰው ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ማድረግ ካስፈለገ የሚከተሉትን ፬ ጥንቃቄዎች መከተል ያስፈልጋል።
  • የኤድስ ቫይረስ ያለባቸው የተለያዩ የኣባለ ዘር ፍሳሾች (Semen, vaginal secretions) ወደ ሌላ ሰው (ብልት፣ ኣፍ፣ ፊንጢጣ ወዘተ...) እንዳይገቡ መጠንቀቅ።
  • የኤድስ መኖር ካጠራጠረ የግብረ ሥጋው ግንኙነት ከመጀመሩ በፊት ወንድየው የላቴክስ (Latex) ላስቲክ ኮንዶም ብልቱ ላይ ማድረግ ኣለበት። ከቆዳ የሚሠራው ዓይነት ኮንዶም ለኤድስ መከላከያ ኣይሠራም።
  • ለተጨማሪ ጥንቃቄ እስፐርሚሳይድስ (Spermicide) ቫይረሶቹን የመግደል ጥቅም ስላላቸው የኮንዶሙን ውጭና ጫፍ ማነካካት ሳይጠቅም ኣይቀርም።
  • ከደረቁ ይልቅ ቅባት (Lubricant) ያለው የላቴክስ ኮንዶም እንዳይቀደድም ይመረጣል። በውሃ (Water-base) በተበጠበጠ እንጂ እንደ ቫስሊን የኣሉ ነዳጅ ዘይት (Oil-based) የሚበጠበጡ ቅባቶች ኮንዶሙን ስለሚበሳሱ ኣለመጠቀም ጥሩ ነው። ፓኬቱ ላይ የተጻፈውን ማንበብ ያስፈልጋል። ከፈቃደ ሥጋው ግንኙነት በኋላ ላቴክሱን በጥንቃቄ ማውጣት መረሳት የለበትም።

ተጨማሪ መረጃ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በተጨማሪም የሚከተሉት ታውቀዋል።

የኣንድ ሰው ደም ወደ ሌላው (በብዛት) ሊተላለፍባቸው የሚችልባቸውን ቍሳቁስ ለሌላ ከማዋስ መቆጠብ። ለምሳሌ ያህል የጺም መላጭያ፣ ጥርስ ብሩሽና መፋቂያ የመሳሰሉትን ኣለመዋዋስ። ደም መበካከልን ሊያስከትሉ የሚችሉ ባህሎች ከኣሉ ማረም ወይም እንዲጠፉ ማበረታታት።

የኤድስ ቫይረስ ሊኖርባቸው የሚችሉ ደምና የመሳሰሉትን ጓንት (እና እንዳስላጊነቱም ማስክ) ሳያደርጉ ኣለመነካካት።

ስለበሽታው ለማያውቁ ማሰማትና ለልጆች ማስተማር እንዲሁም ኤድስ ያለባቸውን በሚቻለን ሁሉ የመርዳት ኃላፊነትና በየጊዜው የሚገኙትን የምርምር ውጤቶች ለማወቅ መሞከርና ይኸንኑ ዕውቀት ማሰራጨት ኣለብን።

የኤድስ ቫይረስ ደካማ በመሆኑ ከኣካል ውጭ ለረዥም ጊዜ ኣይኖርም። (እንደ ዕቃው ዓይነት የተነካኩትን ለዓሥር ደቂቃዎች ማፍላት ወይም ኣንድ በመቶ ብሊች ባለው ውሃ መዘፍዘፍ ቫይረሶቹን ሊገድል ይችል ይሆናል።

ኣንድን ሰው የበሽታው ቫይረስ እንዳላጋጠመው በተለያዩ (ተደጋጋሚ) የደም ምርመራዎች ማጣራት ይቻላል። (ኣስቀድሞም የኣካባቢውን የኤድስ ሕግ ማወቅ ጠቃሚ ነው።)

ኤድስ በመጨባበጥና በመሳሳም እንዲሁም በሽንትና በሰገራ፣ በወባ ትንኝና ቁንጫን በመሳሰሉት ደም መጣጮች ኣይላለፍም ተብሏል።

የኤድስ ቫይረስ (እራሱን ስለሚቀያይር ጥሩ ዓይነት) የመከላከያ ክትባት በቅርቡ ላይሠራ እንሚችል ተተምኗል። የቫይረስ በሽታዎችንም ማዳን በጣም ከባድ ስለሆነ (የኤድስም ቫይረስ ከሰው ጂን ጋር ስለሚካለስ) ፈዋሽ መድኃኒት በቅርቡ መገኘቱ ያጠራጥራል ይባላል። እስከዚያው ድረስ ግን በሽታው በየኣገሩ (ኢትዮጵያ ጭምር) መስፋፋቱን ስለቀጠለ ለሞት ከመማቀቅ ኣስቀድሞ ማወቅ የሚሻል ይመስለኛል። ቫይረሱ (ለረዥም ጊዜ) ከነበረባቸው መካከል ፺፱ በ፻ በበሽታው ተይዘዋል።

AZT (ኤዚቲ) እና የመሳሰሉት መድኃኒቶች ቫይረሱ እንዳይባዛ በመከላከል በሽታው እንዳይገድል ጊዜ ለመግዛት ይጠቅማሉ ይባላል።

የኤድስ መኖር ካጠራጠረ በጥሩ ጤንነት ለመኖር መሞከርና መድንን ከሚያዳክሙ መቆጠብ እንደሚራዱ ተገምቷል።

በሽታው በመካከላችን ስለኣለ በኣለማወቅና በጥንቃቄ ጉድለት በኤድስ ብንያዝ ጥፋቱና ፀፀቱ የራሳችን ይመስለኛል። እስከ (1991) በዩናይትድ እስቴትስ ውስጥ የኤድስ ቫይረስ ከተገኘባቸው ፪፻፸ሺህ ሰዎች መካከል ፩፻ሺህ (፩00, 000) በበሽታው ሞተዋል። በዓለም ላይም (፩፶፬ ኣገሮች) ኣንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በኤድስ በሽታ ተይዘዋል። (ሕዝቡም መጠንቀቅ ካልጀመረ በቫይረሱ የሚበከለው ሰው ቍጥር በየዓመቱ እጥፍ እየሆነ ሊቀጥል እንደሚችልና ለማስታመምም ብዙ ቢሊዮን ዶላርስ እንደሚያስፈልግ ተገምቷል።) ግብረ ሰዶም የሚያዘወትሩና ድረግ የሚወጉ ሰዎች በሽታ ነው እየተባለ ቸል ሲባል ቆይቶ ኣሁን የሁላችንም ጠር መሆኑ ስለተደሰረበት የሚፈለግብንን ብናከናውንና (ከመንግሥታትም ጋር) ብንተባበር በሽታውን መቆጣጠር ይቻል ይሆናል። ፈንጣጣን (እና ደስታ በሽታዎች) ከዓለም ለማጥፋት ከጠቀሙን መካከል ክትባትና የሕዝቡ ትብብር ዋናዎቹ ናቸው። ስለ ግብረ ሥጋ ግንኙነት ማውራት ለማንኛውም ሕብረተሰብ ኣሳፋሪ ቢሆንም ኤድስ ያመጣብን ዱብ-ዕዳ የሕይወት ጉዳይ ስለሆነ መወያየት መጀመር ኣለብን።

ይህ ጽሑፍ የተጻፈው የሕክምና ዕርዳታ ለመስጠት ኣይደለም። በበለጠ ለመረዳት ሓኪሞቻችሁን ኣማክሩ። በ1988 እ.ኤ.አ. ለእያንዳንዱ የዩናይትድ እስቴትስ ቤተሰብ Understanding AIDS የተባለ ፰ ገጽ ጽሑፍ ከU.S. Department of Health and Human Services ሲላክ ወደ አማርኛ በነፃ በዶ/ር ኣበራ ሞላ ተተርጕሞና ተሰራጭቶ ነበር። የእዚህ የ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ጽሑፍ [1] መነሻ ይኸው የHHS Publication No. (CDC) HHS 88-8404 ጽሑፍ ነው። [2]

የውጭ መያያዣዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. አበሻ ኬር የበጎ እድራጊ ድርጅት [3] Archived ፌብሩዌሪ 29, 2008 at the Wayback Machine 2008
  2. Divisions of HIV/AIDS Prevention / October 20, 2008 [4] ትርጒም በአበሻ ኬር
  3. Dr. Aberra Molla in the March and April, 1991 G.C. [ኤድስ በዶክተር ኣበራ ሞላ ፲፱፻፹፫ ዓ.ም.][5] Archived ሜይ 8, 2006 at the Wayback Machine
  4. ዝምታው ይሰበር [6] Archived ማርች 1, 2008 at the Wayback Machine2008
  5. [7] የኢትዮጵያ ኤድስ መረጃ ማእከል
  6. [8]2006-8
  7. [9] ዶ/ር ኣበራ ሞላ AIDS in Amharic, 1991
  8. [10] Understanding AIDS, 1988