ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ሚያዝያ 21

ከውክፔዲያ
  • ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - አዶልፍ ሂትለር እና የብዙ ዘመን ውሽማው ኤቫ ብሮን በበርሊን ምሽግ ውስጥ ተጋቡ። ሂትለር አድሚራል ካርል ዶኒትዝን የሥልጣን ተተኪው እንደሆነ አስታወቀ።
  • ፲፱፻፹፫ ዓ/ም - ‘ቺታጎንግ’ በተባለ የደቡብ-ምሥራቅ የባንግላዴሽ ግዛት ላይ የተነሳ አውሎ-ነፋስ መቶ ሰላሳ ስምንት ሺ ሰዎችን ሲገድል እስከ አሥር ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የመኖሪያ ቤታቸው ወድሞባቸዋል።