ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/የካቲት 21

ከውክፔዲያ

የካቲት ፳፩

  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት በአዋጅ ቁጥር ፪፻፷፩/፶፪ መሠረት ፀደቀ። የድርጅቱ ማቋቋሚያ የአደራ መስጫ ሰነድ (ቻርተር) በሐምሌ ፲፭ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓ/ም በመንግሥት ማስታወቂያ ቁጥር ፪፻፶፫/፶፩ መሠረት ወጥቶአል። ይህ ድርጅት በጥቅምት ወር ፲፱፻፷፮ ዓ/ም የደርግ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት በአዋጅ እስከወረሰው ድረስ አገልግሏል።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ለሰባት ዓመታት ተቋርጦ የነበረው የአሜሪካ እና ግብጽ የዲፕሎማቲክ ግንኙነት እንደገና ጀመረ።
  • ፳፻፭ ዓ/ም - የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ፖፕ ቤኔዲክት ፲፮ኛ «የዕድሜያቸው መግፋት የተደራረበ ሓላፊነታቸውን በአግባቡ ለመወጣት ስላላስቻላቸውና በሚታይባቸው አካላዊ ድካምና አቅም ማጣት» በሚል ምክንያት ሥልጣናቸውን ለቀቁ።