ዓለም ንግድ ሕንጻ

ከውክፔዲያ
ዓለም ንግድ ሕንጻ

የዓለም ንግድ ሕንጻ (World Trade Center) በኒው ዮርክ ከተማ የነበሩ ሰባት ሕንጻዎች ነው። ሕንጻዎቹን የነደፈው ጃፓናዊ-አሜሪካዊው ሚኖሩ ያማሳኪ ነው። 110 ፎቅ ላላቸው መንታ ሕንጻዎቹ ይታወቃል። የየካቲት 19 ቀን 1985 ዓ.ም. ጥቃት ቢቋቋምም በመስከረም 1 ቀን (ሴፕቴምበር 11) 1994 በደረሰበት ጥቃት ፈርሷል።

መግለጫ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሕንጻዎቹ በ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. የተገነቡ ሲሆን በመጋቢት 26 ቀን 1965 ነው የተከፈቱት። በማንኛውም ቀን 50 ሺህ ሠራተኞች ሲኖሩ 200 ሺህ ጎብኚዎችም በየቀኑ አሉ።

ስሙ አንደሚገልጸው በዓለም አቀፍ ንግድ ለተሰማሩ ድርጅቶች የተሰራ ቢሆንም በመጀመሪያ ዓመቶቹ የመንግሥት ቢሮዎችን ነው በብዛት የያዘው። የግል ድርጅቶች ወደ ሕንጻው የገቡት ከ1980ዎቹ ጀምሮ ነው።