ዓሳ ጥብስ
ዓሳ ጥብስ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰራ የምግብ አይነት ሲሆን፣ የሚሰራውም ከዓሳ ነው።
አስፈላጊ ጥሬ ዕቃዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- 800 ግራም ናይል ፐርች
- 1 የሻይ ማንኪያ ጨው
- 1 የሻይ ማንኪያ ቁንዶ በርበሬ
- 4 የቡና ስኒ (200 ግራም) የፉርኖ ዱቄት
- ግማሽ ሊትር ዘይት
- 2 መካከለኛ ሎሚ
አዘገጃጀት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- 1. ዓሣውን በደንብ አፅድቶና አራት ቦታ ከፍሎ የሎሚ ጭማቂውን በሁሉም በኩል ማፍሰስ፤
- 2. ጨው፣ ቁንዶ በርበሬና የፉርኖ ዱቄቱን ቀላቅሎ ዓሣውን ውስጡ እያገላበጡ መለወስ፤
- 3. በጋለ ዘይት ዱቄቱን እያራገፉ መጥበስ፣
- 4. የተጠበሰው ዓሳ ካሮት፣ ጐመን፣ የድንች ጥብስና ሎሚ አጅበውት ሊቀርቡ ይችላሉ። ዓሣው ሲጠበስ በርከት ያለ ዘይት ከተጠቀሙ ዓሣውን ጠብሰው ካበቁ በኋላ ዘይቱን አቀዝቅዞ ለሌላ ጊዜ የዓሣ ምግቦች ሲያዘጋጁ መጠቀም ይቻላል፡፡]
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |