ዘመነ መሳፍንት

ከውክፔዲያ

ዘመነ መሳፍንትኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ እስከ ፲፱ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ የተከሰተ ጊዜ ሲሆን፣ በወቅቱ የየአካባቢው መሳፍንት ኃይል የገነነበትና እርስ በርሳቸው የሚዋጉበት እንዲሁም ዋናው ንጉስ ሥልጣኑ ከመዳከሙ የተነሳ ከጎንደር ከተማ ውጭ እምብዛም ተሰሚነት ያልነበርበት ወቅት ነበር። ከነበረው አለመረጋጋትተነሳ ከጎንደር ከተማ ተነስቶ እየተስፋፋ የነበረው ስልጣኔ የኮሰመነበት፣ እንዲሁም ህብረተሰቡና ባህሉ ወደፊት አንድ እርምጃ መራመድ አቅቶት እየበሰበሰ የነበርበት ወቅት ነው። ከትውፊት አንጻር የዚህ ዘመን ጅማሬ የሚቆጠረው ራስ ሚካኤል ስሑል ዳግማዊ ዓፄ ኢዮአስሚያዝያ ፳፱ ቀን ፲፯፻፷፩ ዓ.ም. ሲያስገድለው ሲሆን በተቃራኒው የዘመኑ ፍጻሜ ዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ የካቲት ፬ ቀን ፲፰፻፵፯ ዓ.ም ንጉሠ ነገሥት ሆነው ስል፧ቾጣን ላይ ሲወጡ ነው።


ራስ ቢትወደድ የሚለውን ስም፡ለማግኘት የነበረ ጦርነት ነው==ዋቢ መጽሕፍት===