ዘመነ መሳፍንት
Jump to navigation
Jump to search
ዘመነ መሳፍንት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከ፲፰ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ እስከ ፲፱ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ የተከሰተ ጊዜ ሲሆን፣ በወቅቱ የየአካባቢው መሳፍንት ኃይል የገነነበትና እርስ በርሳቸው የሚዋጉበት እንዲሁም ዋናው ንጉስ ሥልጣኑ ከመዳከሙ የተነሳ ከጎንደር ከተማ ውጭ እምብዛም ተሰሚነት ያልነበርበት ወቅት ነበር። ከነበረው አለመረጋጋት የተነሳ ከጎንደር ከተማ ተነስቶ እየተስፋፋ የነበረው ስልጣኔ የኮሰመነበት፣ እንዲሁም ህብረተሰቡና ባህሉ ወደፊት አንድ እርምጃ መራመድ አቅቶት እየበሰበሰ የነበርበት ወቅት ነው። ከትውፊት አንጻር የዚህ ዘመን ጅማሬ የሚቆጠረው ራስ ሚካኤል ስሑል ዳግማዊ ዓፄ ኢዮአስን ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፲፯፻፷፩ ዓ.ም. ሲያስገድለው ሲሆን በተቃራኒው የዘመኑ ፍጻሜ ዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ የካቲት ፬ ቀን ፲፰፻፵፯ ዓ.ም ንጉሠ ነገሥት ሆነው ስልጣን ላይ ሲወጡ ነው።
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |