የሐዋርያት ሥራ ፩

ከውክፔዲያ
የሐዋርያት ሥራ ፩
የዋርያት ሥራ ፲፭ ፳፪ ፳፬ በኮዴክ ላውዲያነስ (Codex Laudianus) በ፭፻፶ ዓ ም የተጻፈ
የዋርያት ሥራ ፲፭ ፳፪ ፳፬ በኮዴክ ላውዲያነስ (Codex Laudianus) በ፭፻፶ ዓ ም የተጻፈ
አጭር መግለጫ
ፀሐፊ ቅዱስ ሉቃስ
የመጽሐፍ ዐርስት የሐዋርያት ሥራ
የሚገኘው በአዲስ ኪዳን ፭ኛው መጽሐፍ
መደብ የቤተክርስቲያን ታሪክ
የጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት


የሐዋርያት ሥራ ፩ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲሆን የሚያተኩረው በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርገትና እስከ ጰራቅሊጦስ (መንፈስ ቅዱስ) መምጣት በፊት ሐዋርያት የሠሩት መንፈሳዊ ተግባራት ናቸው ። የጻፈውም ቅዱስ ሉቃስ እንደሆነ በማስረጃ ሙሉበሙሉ ቤተክርስቲያን የምታምነው ነው ይህም በ፳፮ ንዑስ ክፍሎች ይካተታል ።


ኢየሩሳሌም
የቅዱስ እንድሪያስ ቤተክርስቲያን
ኢየሩሳሌም
የሐዋርያት ሥራ ፩ is located in
ቤተልሔም
ቢታኒያ
ደበረ ዘይት
ቅዱስ ሉቃስ የሐዋርያትን ሥራ የጻፈባት ቅድስት ከተማ ኢየሩሳሌም አካባቢዋ ።


የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፩

ቁጥር ፩ - ፲[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

1-2፤ቴዎፍሎስ፡ሆይ፥ኢየሱስ፡የመረጣቸውን፡ሐዋርያትን፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ካዘዛቸው፡በዃላ፡ እስከዐረገበት፡ ቀን፡ድረስ፥ያደርገውና፡ያስተምረው፡ዘንድ፡ስለዠመረው፡ዅሉ፡ መዠመሪያውን፡ነገር፡ጻፍኹ፤ 3፤ደግሞ፡አርባ፡ቀን፡እየታያቸው፡ስለእግዚአብሔርም፡ መንግሥት፡ነገር፡እየነገራቸው፥በብዙ፡ማስረጃ፡ከሕማማቱ፡በዃላ፡ሕያው፡ኾኖ፡ለእነርሱ፡ ራሱን፡አሳያቸው። 4፤ከነርሱም፡ጋራ፡ዐብሮ፡ሳለ፡ከኢየሩሳሌም፡እንዳይወጡ፡አዘዛቸው፥ ነገር፡ግን፦ከእኔ፡የሰማችኹትን፡አብ፡የሰጠውን፡የተስፋ፡ቃል፡ጠብቁ፤ 5፤ዮሐንስ፡በውሃ፡ አጥምቆ፡ነበርና፥እናንተ፡ግን፡ከጥቂት፡ቀን፡በዃላ፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ትጠመቃላችኹ፡ አለ። 6፤እነርሱም፡በተሰበሰቡ፡ጊዜ፦ጌታ፡ሆይ፥በዚህ፡ወራት፡ለእስራኤል፡መንግሥትን፡ ትመልሳለኽን፧ብለው፡ጠየቁት። 7፤ርሱም፦አብ፡በገዛ፡ሥልጣኑ፡ያደረገውን፡ወራትንና፡ ዘመናትን፡ታውቁ፡ዘንድ፡ለእናንተ፡አልተሰጣችኹም፤ 8፤ነገር፡ግን፥መንፈስ፡ቅዱስ፡ በእናንተ፡ላይ፡በወረደ፡ጊዜ፡ኀይልን፡ትቀበላላችኹ፥በኢየሩሳሌምም፡በይሁዳም፡ዅሉ፡ በሰማርያም፡እስከምድር፡ዳርም፡ድረስ፡ምስክሮቼ፡ትኾናላችኹ፡አለ። 9፤ይህንም፡ከተናገረ፡ በዃላ፡እነርሱ፡እያዩት፡ከፍ፡ከፍ፡አለ፤ደመናም፡ከዐይናቸው፡ሰውራ፡ተቀበለችው። 10፤ርሱም፡ሲኼድ፡ወደ፡ሰማይ፡ትኵር፡ብለው፡ሲመለከቱ፡ሳሉ፥እንሆ፥ነጫጭ፡ልብስ፡ የለበሱ፡ኹለት፡ሰዎች፡በአጠገባቸው፡ቆሙ፤

ቁጥር ፲፩ - ፳[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

11፤ደግሞም፦የገሊላ፡ሰዎች፡ሆይ፥ወደ፡ሰማይ፡እየተመለከታችኹ፡ስለ፡ምን፡ቆማችዃል፧ ይህ፡ከእናንተ፡ ወደ፡ሰማይ፡የወጣው፡ኢየሱስ፡ወደ፡ሰማይ፡ሲኼድ፡እንዳያችኹት፥እንዲሁ፡ ይመጣል፡አሏቸው። 12፤በዚያን፡ጊዜ፡ደብረ፡ዘይት፡ከሚባለው፡ተራራ፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ ተመለሱ፥ርሱም፡ከኢየሩሳሌም፡የሰንበት፡መንገድ፡ያኽል፡የራቀ፡ነው። 13፤በገቡም፡ጊዜ፡ ወደሚኖሩበት፡ሰገነት፡ወጡ፥ጴጥሮስና፡ ዮሐንስም፣ያዕቆብም፣እንድርያስም፣ፊልጶስም፣ ቶማስም፣በርተሎሜዎስም፣ማቴዎስም፣የእልፍዮስ፡ልጅ፡ያዕቆብም፣ቀናተኛ፡የሚባለው፡ ስምዖንም፣የያዕቆብ፡ልጅ፡ይሁዳም። 14፤እነዚህ፡ዅሉ፡ከሴቶችና፡ከኢየሱስ፡እናት፡ ከማርያም፡ከወንድሞቹም፡ጋራ፡ባንድ፡ልብ፡ኾነው፡ለጸሎት፡ይተጉ፡ነበር። 15፤በዚህም፡ወራት፡ጴጥሮስ፡መቶ፡ኻያ፡በሚያኽል፡በሰዎች፡ማኅበር፡ዐብረው፡በነበሩ፡ በወንድሞቹ፡መካከል፡ተነሥቶ፡አለ፦ 16፤ወንድሞች፡ሆይ፥ኢየሱስን፡ለያዙት፡መሪ፡ ስለኾናቸው፡ስለ፡ይሁዳ፡መንፈስ፡ቅዱስ፡አስቀድሞ፡በዳዊት፡አፍ፡የተናገረው፡የመጽሐፍ፡ ቃል፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ይገ፟ባ፟፡ነበር፤ 17፤ከእኛ፡ጋራ፡ተቈጥሮ፡ነበርና፥ለዚህም፡አገልግሎት፡ ታድሎ፡ነበርና። 18፤ይህም፡ሰው፡በዐመፅ፡ዋጋ፡መሬት፡ገዛ፥በግንባሩም፡ተደፍቶ፡ከመካከሉ፡ ተሰነጠቀ፥አንዠቱም፡ዅሉ፡ተዘረገፈ፤ 19፤በኢየሩሳሌምም፡ለሚኖሩ፡ዅሉ፡ታወቀ፤ ስለዚህም፡ያ፡መሬት፡በቋንቋቸው፡አኬልዳማ283፡ተብሎ፡ተጠራ፥ርሱም፡የደም፡መሬት፡ ማለት፡ነው። 20፤በመዝሙር፡መጽሐፍ፦መኖሪያው፡ምድረ፡በዳ፡ትኹን፥የሚኖርባትም፡ አይኑር፤ደግሞም፦ሹመቱን፡ሌላ፡ይውሰዳት፡ተብሎ፡ተጽፏልና።

ቁጥር ፳፩ - ፳፮[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

21-22፤ስለዚህ፥ከዮሐንስ፡ጥምቀት፡ዠምሮ፥ከእኛ፡ዘንድ፡እስካረገበት፡ቀን፡ድረስ፥ጌታ፡ ኢየሱስ፡በእኛ፡መካከል፡በገባበትና፡በወጣበት፡ዘመን፡ዅሉ፥ከእኛ፡ጋራ፡ዐብረው፡ከነበሩት፡ ሰዎች፥ከነዚህ፡አንዱ፡ከእኛ፡ጋራ፡የትንሣኤው፡ምስክር፡ይኾን፡ዘንድ፡ይገ፟ባ፟ል። 23፤ኢዮስጦስም፡የሚሉትን፡በርስያን፡የተባለውን፡ዮሴፍንና፡ማትያስን፡ኹለቱን፡አቆሙ። 24-25፤ሲጸልዩም፦የዅሉን፡ልብ፡የምታውቅ፡አንተ፡ጌታ፡ሆይ፥ይሁዳ፡ወደገዛ፡ራሱ፡ስፍራ፡ ይኼድ፡ዘንድ፡በተዋት፡በዚች፡አገልግሎትና፡ሐዋርያነት፡ስፍራን፡እንዲቀበል፡የመረጥኸውን፡ ከነዚህ፡ከኹለቱ፡አንዱን፡ሹመው፡አሉ። 26፤ዕጣም፡ተጣጣሉላቸው፥ዕጣውም፡ለማትያስ፡ ወደቀና፡ከዐሥራ፡አንዱ፡ሐዋርያት፡ጋራ፡ተቈጠረ።