የአካዳውያን ታላቅ መፈንቀል

ከውክፔዲያ

የአካዳውያን ታላቅ መፈንቀል1747 እስከ 1755 ዓ.ም. ድረስ የእንግሊዝ መንግሥት በአካዲያ ፈረንሳዊ ሕዝብ ላይ ብግድ የጣለው ስደት ነበር።

ፈረንሳውያን ከ1596 ዓ.ም. ጀምሮ «አካዲ» (አካዲያ ወይም የዛሬው ኖቫ ስኮሺያካናዳ) በተባለ አውራጃ ከኗሪ ሚግማቅ ሕዝብ ጋራ አንድላይ ይኖሩ ነበር። አገሩ ለረጅም ዘመናት የሚግማቅ መኖሪያ ምንም ቢሆንም በ1705 ዓ.ም. የፈረንሳይ ንጉሥ በአንድ የአውሮፓ ጦርነት ድል ሆኖ በኢውትረኽት ውል ስምምነት ሥር ቅኝ አገሩን (አካዲያ) ለእንግሊዝ ሀብት ሰጠ። ከዚህ ጀምሮ የእንግሊዝ መንግሥት በዙሪያው የኖሩት ሕዝቦች እንደ ገዛው ተገዦች ቆጠራቸው። በ1746 ዓ.ም. ግን እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ወደ ጦርነት ስለ ተመለሡ፣ እንግሊዝ ከነዚህ ተገዦች የተነሣ ስለ ታማኝነታቸው ብዙ ስለ ፈራ፣ ሚግማቆቹን እየገደላቸው ከ14,000 በላይ ፈረንሳያውያንን (አካዲያውያንን) ከቤቶቻቸው ወደ ሌላ ቅኝ አገሮቹ በግፍ አሳደዳቸው። ከነዚህ ብዙዎች በሉዊዚያና ቅኝ አገር ፈልሰው እስከ ዛሬ ድረስ ካጀን («አካድየን» ወይም አካዲያዉያን) የሚባል ሕዝብ በሉዊዚያና ይገኛል።