Jump to content

ዳሞት ፑላሳ

ከውክፔዲያ


ዳሞት ፑላሳ
Damoota Pullaasa
ወረዳ
ሀገር ኢትዮጵያ
ክልል ደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት
ዞን ወላይታ ዞን
ርዕሰ ከተማ ሻንቶ

ዳሞት ፑላሳ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በወላይታ ዞን ሚገየኝ ወረዳ ነው። ዳሞት ፑላሳ ወረዳ በምስራቅ እና በደቡብ በዳሞት ጋሌ በምዕራብ በቦሎሶ ሶሬ እና በሰሜን ከሀዲያ ዞን ይዋሰናል። ዳሞት ፑላሳ በ1998 ዓ.ም ከዳሞት ጋሌ ወረዳ ተለይቷል። የወረዳው አስተዳደር ማዕከል ሻንቶ ከተማ ነው።

የስነ ሕዝብ አወቃቀር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እ.ኤ.አ 2019 በማዕከላዊ እስታቲስቲክ ኤጀንሲ በተካሄደው የህዝብ ብዛት ትንበያ መሰረት [1] ይህ ወረዳ በድምሩ 135,760 ህዝብ ያለው ሲሆን ከነዚህም 66,463 ወንዶች እና 69,297 ሴቶች ናቸው። 5,346 ወይም 5.08% የሚሆነው የወረዳው ህዝብ የከተማ ነዋሪ ነው። አብዛኛው ነዋሪ ፕሮቴስታንቶች ሲሆን፣ 73.72% የሚሆነው ህዝብ ይይዛል፣ የሮማ ካቶሊክ እምነት ተከታዮች ደግሞ 17.1% ይይዛል፣ እና 8.17% የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ናቸው።

ዋቢ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]