ዳዱሻ

ከውክፔዲያ

ዳዱሻመስጴጦምያኤሽኑና ንጉሥ ነበረ (1712-1692 ዓክልበ. የነገሠ)። የ2 ኢፒቅ-አዳድ ልጅና የዳኑም-ታሃዝ ተከታይ ነበረ።

የዳዱሻ ዘመነ መንግሥት ከዓመት ስሞቹ መሃል ፱ ያህል ከሥነ ቅርስ ተገኝተዋል።[1] ቀደም-ተከተላቸው ግን አይታወቅም። ከነዚህ መካከል፦

1712 ዓክልበ. - «ዳዱሻ በአባቱ በት የገባበት ዓመት»
b. - «ዳዱሻ የኤካላቱም ሠራዊት ያሸነፈበት ዓመት»
g. - «ዳዱሻ ማንኪሱምን የያዘበት ዓመት።»
1692 ዓክልበ. - «ዳዱሻ ቃባሩምን የያዘበት ዓመት።»

በዚህ ዘመን ማንኪሱምና ኤካላቱም የ1 እሽመ-ዳጋን ግዛቶች ነበሩ፤ ይህም አባቱ 1 ሻምሺ-አዳድአሦር ንጉሥ እየሆነ ነው። የእሽመ-ዳጋን ደብዳበዎች ስለዚህ ዘመቻ ይታወቃሉ። በ1694 ዓክልበ. ዳዱሻ ከሻምሺ-አዳድ ጋራ በሰላም ተስማምቶ አብረው በአርቤላ ላይ ዘመቱ። «የዳዱሻ ጽላት» በመጨረሻው ዓመት ዳዱሻና ሻምሺ-አዳድ በአርቤላና ቃባሩም ንጉሥ ቡኑ-እሽታር ላይ ያደረጉትን ዘመቻ ይተርካል። የቡኑ-እሽታር ግዛት በሱባርቱዛብ ወንዝ ነበረ።

በአንዳንድ መምህር አስተሳሰብ ዳዱሻ የኤሽኑና ሕግጋት ያወጣቸው ንጉሥ ነው። ልጁም 2 ኢባልፒኤል ተከተለው።

ቀዳሚው
ዳኑም-ታሃዝ
ኤሽኑና ንጉሥ
1712-1692 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
2 ኢባልፒኤል

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ የዳዱሻ ዓመት ስሞች