Jump to content

ጌትነት ተስፋማርያም

ከውክፔዲያ

ጋዜጠኛ ጌትነት ተስፋማርያም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እና በተለያዩ ጦማሮች ላይ የሚፅፉ ጋዜጠኛ ናቸው።[1]

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በጋዜጠኝነት እና ኮሚኒኬሽን የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስኩል ኦፍ ኮሜርስ በሎጂስቲክስ ማናጅመንት ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በጥሩ ውጤት አጠናቀዋል።

ጋዜጠኛ ጌትነት ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በጋዜጠኝነት እንዲሁም በኢትዮ ቴሎኮም በፐብሊክ ሪሌሽንስ ኤክስፐርትነት አገልግለዋል።

ጋዜጠኛ ጌትነት ከ11 ዓመት በላይ በሰሩባቸው የተለያዩ ወቅቶች በርካታ ፅሁፎችን እና ጦማሮችን አዘጋጅተዋል።

ከፃፏቸው መካከል በየፋርማሲው በግላጭ የሚቸበቸበው ትውልድ አደንዛዥ፣ ህዝቡን ማማረር እስከመቼ፣ ሁሉም ለስብሰባ አዳማ ናቸው የሚባልበት ተቋም ፣ የአፄ ቴዎድሮስን 150ኛ ዓመት አስመልክቶ የተለያዩ አንዶችን እና በርካታ ዘገባዎችን አቅርበዋል።

ጋዜጠኛ ጌትነት ተስፋማርያም በአዲስ አበባ ተወልደው እየሰሩ የሚገኙ ኢትዮጵያዊ ናቸው።

  1. Getnet Tesfamariam
    • ሁሉም ለስብሰባ አዳማ ናቸው የመባልበት ተቋም
    • ባለከዘራው ኮሎኔል
    • በግላጭ በየፋርማሲው የሚቸበቸበው ትውልድ አደንዛዣ መድኃኒት
    • ህዝብን ማማረር እስከመቼ ...