ፋሲል ግምብ

ከውክፔዲያ
(ከፋሲለደስ ግምብ የተዛወረ)
ፋሲል ግምብ በ1894ዓ.ም.

ፋሲል ግምብ ፋሲል ግቢ ውስጥ ካሉት ግምቦች ትልቁና ቀደምቱ ነው። አጼ ፋሲለደስ የአገሪቱ መዲናን ከቦታ ቦታ መዛወር በመሰልቸት በመጨረሻ ጎንደር ከተማ ላይ የረጋ ማዕከል በ1628ዓ.ም. አቋቋሙ። በ1640ወቹ መጀመሪያ ፋሲል ግምብን በከተማው ማዕከል አሰርተው አስጨረሱ። ፋሲል፣ ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች ግምቦችንና ከ7 የማያንሱ ቤተክርስቲያኖችን እንዲሁም 7 ድልድዮችንና የአክሱም ጽዮንን ግንብ አሰርተዋል።

ፋሲል ግምብ ፋሲል ግቢ ውስጥ በስተ ደቡብ የተቀመጠ ሲሆን ሁለት ፎቅና 123 ደረጃዎች አሉት። ከጣሪያው ላይ ባለው መመልከቻ በረንዳ እስከ ጣና ሐይቅ ድረስ መመልከት ይቻላል። በውስጡ 20 ክፍሎች ሲኖሩት ከላይ የሚገኙት ክብ ክፍሎች ለጸሎትና መሰል የሃይማኖት ስራዎች ይጠቅም ነበር። ከላይ ያለው ጠፍጣፋው ክፍል ንጉሱ ለህዝቡ የሚናገሩበት ነበር፡

ፋሲል ግምብ በአሁኑ ዘመን