ፋሺዝም

ከውክፔዲያ

ፋሺዝም የፖለቲካዊ ርዕዮት ዓለም ሆኖ ሥልጣናዊነትን እና ጽንፈኛ ብሔርተኝነትን አዋህዶ የያዘ ነው። ከፋሽዝም መገለጫዎች ውስጥ፣ ፈላጭ ቆራጭነት፣ ተቃራኒ ሐሳቦችንም ሆነ ማሕበረሰቦች በፍጹም ማፈን፣ ኢኮኖሚውንና ማህበረሰቡን ደግሞ ዝንፍ በማይል ሥነ-ሥርዓት ማስተዳደር ይጠቀሳሉ። የፋሽዝም ኣባት እና ደራሲ የጣሊያኑ መሪ ቤኔቶ ሞሶሊኒ ነው።