ፎጣድ ካይርፕተቅ እና ፎጣድ አይርግጠቅ

ከውክፔዲያ

ፎጣድ ካይርፕተቅ እና ፎጣድ አይርግጠቅ279 እስከ 280 ዓም ድረስ የአየርላንድ ጋርዮሽ ከፍተኛ ነገሥታት ነበሩ። ሁለቱ ፎጣዶች ደግሞ ወንድሞች ነበሩ።

በአይርላንድ ታሪኮች ዘንድ ቀዳሚያቸው ካይርብሬ ሊፌቃይር ከተገደለ በኋላ፣ ለአንድ አመት ከፍተኛ ንጉሥነቱን በጋራ ያዙ፤ ከዚያ ግን ፎጣድ አይርግጠቅ ወንድሙን ገደለ እና ካይልቴ ማክ ሮናይን አይርግጠቅን ገደለው። ከዚያ ፍያቃ ስሮይፕቲኔ ከፍተኛ ንጉሥ ሆነ።

የቲገርናቅ ዜና መዋዕል (1080 ዓም ተቀነባብሮ) ፎጣዶቹን አይጠቅስም። የካይርብሬ ዘመን በ253 ዓም እንደ ጀመረ፣ ለ25 ዓመታት እንደ ቆየ ይዘግባል። (ሌሎቹ ምንጮች ካይርብሬን 26 ዓመታት ይሰጡታል)። የፍያቃም ዘመን በ280 እንደ ጀመረ ሲለን በዚህ አቆጣጠር የፎጣዶች ዓመት 279-280 ዓም መሆን አለበት።