ፖርት ኦፍ ስፔን

ከውክፔዲያ

ፖርት ኦፍ ስፔንትሪኒዳድና ቶቤጎ ዋና ከተማ ነው።

ከወደቡ ስትታይ ከኤሪክ ዊሊያም ፒያሥ መንታ ፎቆች አጠገብ

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 263,800 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 45,300 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 10°38′ ሰሜን ኬክሮስ እና 61°31′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

በደሴቱ የነበሩ ኗሪዎች በሥፍራው 'ኩሙኩራፖ' የተባለ መንደር ነበራቸው። በ1530ዎቹ ስፓንያውያን እንዲሠፈሩት አንዳንድ ሙከራዎች አድርገው ስሙን 'ፕዌርቶ ዴ እስፓንያ' (የእስፓንያ ወደብ) አሉት። ነገር ግን ሠፈሩ ቋሚ አልሆነም። በ1552 ዓ.ም. የእስፓንያ ወታደሮች ምሽግ በዚያ አካባቢ ሰሩ። ከተማ እራሱ ግን በ1682 ዓ.ም. ገዳማ ሊገነባ ጀመረ። በ1749 ዓ.ም. የደሴቱ መቀመጫ ከ'ሳን ሆዜ ዴ ኦሩኛ' (የዛሬው ሰይንት ጆሴፍ) ወደዚህ ተዛወረ።