4 ሰኑስረት

ከውክፔዲያ
ሰኑስረት 4 ሰነፈሪብሬ
የሰኑስረት ሰነፈሪብሬ ሐውልት
የሰኑስረት ሰነፈሪብሬ ሐውልት
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1592 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ መራንኽሬ 6 መንቱሆተፕ ?
ተከታይ 2 ደዱሞስ
ሥርወ-መንግሥት 16ኛው ሥርወ መንግሥት


ሰነፈሪብሬ 4 ሰኑስረትላይኛ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን (16ኛው ሥርወ መንግሥት) ምናልባት 1592 ዓክልበ. አካባቢ የገዛ ፈርዖን ነበረ።

ስሙ የሚታወቅ ከአንድ ትልቅ ሐውልት፣ በ1ኛው ዓመት ከተቀረጸ ጽላትና ከአንዳንድ ጥቃቅን ቅርሶች ነው። ከዚህ በላይ በካርናክ ዝርዝር ላይ «ሰነፈር<...>ሬ» የተባለ ፈርዖን ይገኛል።

ቶሪኖ ቀኖና ዝርዝር ላይ ከሰኸምሬ ሸድዋሰት ቀጥሎ አምስት የፈርዖን ስሞች ጠፍተዋል። በአቶ ኪም ራይሆልት አስተሳሰብ ሰነፈሪብሬ በነዚህ አምስት መካከል ነበሩ።


ቀዳሚው
መራንኽሬ 6 መንቱሆተፕ
ግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን
1592 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
2 ደዱሞስ