ከ«የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፮» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
Added links Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit |
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
||
መስመር፡ 4፦ | መስመር፡ 4፦ | ||
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]] |
|image=[[ስዕል:ፀሎተ ሐሙስ.jpeg]] |
||
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
[[File:Livre.png|88px]]</div></h1> |
||
|data1=<span style=color:blue>ዘቅዱስ ሕርያቆስ</span> |
|||
}}</center> |
}}</center> |
||
<br>፴፪ ፤ <span style=color:red>የሙሴ ጽላት ጳጦስ </span>የተባለች የሲና ዕፅ በካህን አሮን ልብስ የነበረች ጸናጽል ዳግመኛም የበቀለችና ያበበች ያፈራችም በትር አንቺ ነሽ ። |
<br>፴፪ ፤ <span style=color:red>የሙሴ ጽላት ጳጦስ </span>የተባለች የሲና ዕፅ በካህን አሮን ልብስ የነበረች ጸናጽል ዳግመኛም የበቀለችና ያበበች ያፈራችም በትር አንቺ ነሽ ። |
በ07:01, 12 ኦክቶበር 2021 የታተመው ያሁኑኑ እትም
የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፮ | |
---|---|
ዘቅዱስ ሕርያቆስ |
፴፪ ፤ የሙሴ ጽላት ጳጦስ የተባለች የሲና ዕፅ በካህን አሮን ልብስ የነበረች ጸናጽል ዳግመኛም የበቀለችና ያበበች ያፈራችም በትር አንቺ ነሽ ።
፴፫ ፤ የእያሱ የምስክሩ ሐውልት ፣ የጌድዮን ፀምር ፣ የሳሙኤል የሽቱ ሙዳይና የዘይት ቀንድ አንቺ ነሽ ። የተመካባት የዕሴይ ሥር የአሚናባድም ሠረገላ የዳዊት መሰንቆ የሰለሞንም አክሊል አንቺ ነሽ ። የታጠረች ተክል የተዘረጋች የውኃ ጉድጓድ አንቺ ነሽ ።
፴፬ ፤ የኤልያስ የወርቅ መሶብ የኤልሳዕ ጋን አንቺ ነሽ ። ኢሳያስ ፅንስን ከድንግልና ጋር የተናገረልሽ ዳንኤልም ያለ ሩካቤ መውለድን የተናገረልሽ አንቺ ነሽ ።
፴፭ ፤ ፋራን የምትባል የዕንባቆም ተራራ የተዘጋች የሕዝቅኤል ምሥራቅ የቤተ ልሔም ሕግ መውጫ ኤፍራታ የምትባል ምድር አንቺ ነሽ ። የሲሎንዲስ ዕፀ ሕይወት የናሆምንም ቁስል የምታድን የዘካርያስ ደስታው የሚልክያስ ንጹሕት አዳራሽ አንቺ ነሽ ።
፴፮ ፤ ድንግል ሆይ የነብያት ትንቢትና ምሳሌ የሐዋርያት ሞገሳቸው የሰማዕታት እናታቸው የመላእክት እኅታቸው አንቺ ነሽ ። በመዓልትና በሌሊት በበሮችዋ ደጅ የሚጠኑ የወራዙትና የደናግል የመነኮሳትም መመኪያቸው አንቺ ነሽ ።