ኢብሉል-ኢል

ከውክፔዲያ
የማሪና የኤብላ ግዛቶች፣ 2116 ዓክልበ. ግ.

ኢብሉል-ኢል ከ2127-2115 ዓክልበ. ግድም የማሪ ንጉሥ ነበር። የማሪ ጽላቶች የተባሉት ሰነዶች ክምችት ከርሱ ዘመን ጀምሮ ይታወቃል። የኤብላ ግዛት ያንጊዜ በሶርያ አካባቢ ሰፊ ነበር። ኢብሉል-ኢል ግን በተወዳዳሪው በኤብላ ንጉሥ ኢግሪሽ-ሐላብ ላይ ጦርነት እየሠራ ከኤብላ ብዙ መንደሮች ያዘ። በ2115 ዓክልበ. ግ ኢግሪሽ-ሐላብ ሞተና ኢርካብ-ዳሙ ተከተለው። በዚህም ዓመት የኤብላ ጦር አለቃ ኤና-ዳጋን ኢብሉል-ኢል አሸነፈ። ይህ ሁሉ የሚታወቅ ኤና-ዳጋን በዘገበው መረጃ ጽላት ነው። በዚህም ጽላት ኢብሉል-ኢል «የማሪና የአሹር ንጉሥ» ይባላል። (የዛሬው ሊቃውንት ግን አሁን «አሹር» ሳይሆን «አባርሳል» ነው የሚለው ባዮች ናቸው።) ኒዚ ለአጭር ጊዜ ለማሪ ንጉሥነት ቢሾምም በቅርብ ጊዜ ውስጥ ኤና-ዳጋን የማሪ ዙፋን ለራሱ ያዘ። .

ቀዳሚው
ኢቱፕ-ኢሻር
ማሪ ንጉሥ
2127-2115 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ኒዚ