ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ቡድን
ከውክፔዲያ
| ሙሉ ስም | ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክበብ |
| ምሥረታ | ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፳፰ ዓ/ም በአዲስ አበባ |
| ስታዲየም | አዲስ አበባ ስታዲየም |
| ፕሬዝዳንት | አቶ አብነት ገብረመስቀል |
| ሊግ | የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ |
| ድረ ገጽ | ይፋ ድረ ገጽ |
ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ቡድን መቀመጫውን በአዲስ አበባ ያደረገ ሲሆን ዋና ስታዲየሙ የአዲስ አበባ ስታዲየም ነው። ይህ ቡድን የኢትዮጲያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አባል ነው።
ታሪክ [ለማስተካከል]
ቅዱስ ጊዮርጊስ የስፖርት ክበብ የተመሠረተው ጣሊያን ኢትዮጲያን በወረረችበት ጊዜ፣ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፳፰ ዓ/ም በአዲስ አበባ አራዳ አካባቢ ፣ አየለ አጥናሽ እና ጆርጅ ዱካስ በተባሉ ሁለት ግለሰቦች ነው። የኋላ ኋላ ክለቡ የኢትዮጲያ ምልክት እስከመሆን ደርስዋል።
አሸናፊነት [ለማስተካከል]
ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግን በተለያዩ አመታት አሸናፊ ሁንዋል። እነዚህም፦ 1950, 1966, 1967, 1968, 1971, 1975, 1987, 1991, 1992, 1994, 1995, 1996, 1999, 2000, 2002, 2003, 2005, 2006, 2008, 2009 (እ.ኤ.አ.) ናቸው።

