የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ከWikipedia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከአምስቱ የኦርየንታል (ምስራቃዊ) ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክሪስቲያናት አንዱ ነው። ኢትዮጵያ የክርስትናን እምነት ከተቀበለችበት ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ ጥር ፮ ቀን ፲፱፻፵፫ ዓ.ም (1951 እ.ኤ.አ.) ድረስ የእስክንድርያ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን ክፍል ነበር። በ፲፱፻፵፫ ዓ.ም ግን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ባስልዮስ ከእስክንድርያው ፓትርያርክ አቡነ ዮሳብ 2ኛ የጵጵስና ማዕረግ ተቀበሉ። ኢትዮጵያም፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እራሷን የቻለች ሆነች። ወደ 40-45 ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው።
ይዞታ |
[ለማስተካከል] በታሪክ
[ለማስተካከል] መሠረቶች
«ተዋሕዶ» ከልሣነ ግእዝ የመነጨ ቃል ሲሆን፡ ትርጒሙም «አንድ ሆኖ» ማለት ነው። ለዚሁም በዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል «ታውሒድ» ሲባል በአንድ አምላክ ብቻ ማመን የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ያመለክታል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ በ«ሰብዓዊ» እና በ«መለኮታዊ» ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው።
በ443 ዓ.ም. (451 እ.ኤ.አ.) በሮማው ንጉሥ መርቅያን ዘመነ መንግሥት 650 ኤጲስ ቆጶሳት በተገኙበት የተሰበሰበው የኬልቄዶን ጉባኤ ከሮማው ሊቀ ጳጳሳት ቀዳማዊ ልዮን"ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት አሉት" የሚል ጽሑፍ አቅርቦላቸው ነበር። ዳሩ ግን የእስክንድርያው ፓትርያርክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ "ጌታ ሁለት ባሕርያት አሉት" የሚለው ትምሕርት ስሕተት ነው ብሎ ልዮንን አውገዘው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት በእምነት ተለያዩ። የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ትምሕርት የሚከተሉ ዛሬ የአርሜኒያ፣ የሕንደኬ፣ የግብጽ፣ የሶርያ፤ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት ናቸው።
የቤተክርስቲያን መመስረት በኢትዮጵያ የተጀመረው በወንጌል ሰባኪ ቅዱስ ፊልጶስ መሆኑ ይታወሳል (ሐዋርያት ምዕራፍ 8)፦
- «እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሰለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር...»
በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል እንዲገባው አስረድቶት በክርስትና አጠመቀው። ንግሥትግርማዊት ህንደኬ 7ኛ ከ34 ዓ.ም. እስከ 44 ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው።
በ4ኛ ምዕተ ዘመን በወንድማማቾቹ በንጉሥ ኤዛና እና በንጉሥ ሳይዛናዘመን በፍሬምናጦስ አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ «አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን» ተብሎ ይታወቃል። በወጣትነት ዕድሜው ከአጎቱ ከፈላስፋው ከመሮፔዎስ እና ከወንድሙ ከሲድራኮስ ጋራ መርከባቸው ስለሰመጠች ከወንድሙ ጋር ከሞት ተርፈው ምጽዋ አጠገብ ተገኙ። ወደ ንጉሦቹም ግቢ አመጡዋቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበት ደረጃ አገኙ። ንጉስ ኤዛና ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምናጦስን ለኢትዮጵያ አቡነ እንዲሾም ለመጠይቅ ወደ እስክንድርያ ላኩዋቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ አትናቴዎስ ፍሬምናጦስን ሾሞ ላከው። ፍሬምናጦስ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ ደግሞ 111ኛው መሆናቸው ነው።
[ለማስተካከል] መካከለኛ ዘመን
እስላሞች ወደ ግብጽ ከገቡ በኋላ ከእስክንድርያ ጋር የነበረው ግንኙነት ተቸገረ። ጸሐፊው አቡ ሳሊኅ በ12ኛ መቶ ዘመን እንደ ገለጸው፣ ፓትርያርኩ በየዓመቱ 2 ደብዳቤዎች ለኢትዮጵያና ለኖቢያ ነገሥታት ይጽፉ ነበር። ይህንን አደራረግ ግን አቡ ሃኪም አስቀረ። 67ኛው ፓትርያርክ ቂርሎስ እንደ ኤጲስ ቆሞስ የላኩት ሰቨሩስ ሲሆኑ የቤተክርስቲያን ሥራዐት ሁሉ እንዲያስጠበቁ ታዘዙ። በ1431 ዓ.ም. በዓጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ከ1 ፈረንሳያዊ ጐባኝ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስላነጋገሩ አንድ ተልእኮ ወደ ሮማ ተላከ።
በ1500 ዓ.ም. ደግሞ ኢትዮጵያ ከአዳል ጋር ስትታገል ማቴዎስ የተባለ አንድ አርሜናዊ ወደ ፖርቱጋል ተልኮ የፖርቱጋል ንጉሥ እርዳታ ለመነ። ስለዚህ በ1512 ዓ.ም. የፖርቱጋል ሚሲዮን በኢትዮጵያ ደረሰ። በሚከተለው ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋል ኢየሱሳውያን የተባሉ ሚሲዮኖች ቤተ መንግሥቱን ወደ ሮማ ካቶሊክ ሃይማኖት ለማዞር ብዙ ጣሩ። በመጨረሻ በ1617 ዓ.ም. ንጉሥ ሱስንዮስ ወደ ሮማ ካቶሊክ እምነት ተቀየሩ። ዳሩ ግን የሮማ ሃይማኖት በተዋህዶ ፈንታ ይፋዊ መሆኑን ሕዝቡ በጣም አልወደደምና በ1625 ሱስንዮስ ዘውዳቸውን ለልጃቸው ለፋሲለደስ እንዲሰጡ ተደረጉ። ፋሲለደስ ወዲያው አገሩን ወደ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መለሱ። ከዚህ በላይ በ1626 ፋሲለደስ ኢየሱሳውያን አገሩን ለቅቀው እንዲሄዱ አዘዙ። በ1658 ዓ.ም. መጻሕፍታቸውን ደግሞ አስቃጠሉ።
[ለማስተካከል] በቅርብ ጊዜ
[ለማስተካከል] ልዩ ባሕርይ
[ለማስተካከል] የሚቀበሉ ቅዱሳን መጻሕፍት
ኢትዮጵያ ብሉይ ኪዳንንና ሐዲስ ኪዳንን በሙሉ (ከነዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍት ሁሉ በመቀበል ብቸኛ ሃገር ናት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ቁጥራቸው 81 ሲሆን እነዚህም 35 የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትና 46 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ናቸው። ይህ የቅዱሳት መጻሕፍት ቁጥር በቀኖና አበው 318ቱ ሊቃውንት በኒቂያ ገባኤ ተደንግገዋል።
[ለማስተካከል] ልሳነ ቅዳሴና ልሳነ ስብከት
[ለማስተካከል] ሥነ ሕንፃ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሥነ ሕንፃ የቤተክርስቲያናት ትውፊታዊ የሥነ ሕንጻ ጥበብዋ አምስት ዐይነት ነው ። እነርሱም ክብ ፤ መስቀል ቅርፅ ፤ ዋሻ ፤ ፍልፍል እና ስቀልማ ናቸው ። ክብ ሕንጻ አብያተክርስቲያናት በብዛት በገጠሪቷ ኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን ፤ መስቀል ቅርጽ ያላቸው ደግሞ በከተማ አካባቢ ይገኛሉ። ዋሻ አብያተ ክርስቲያናት በብዛት በተራራማ አካባቢዎች ሢገኙ ፤ ፍልፍል አብያተክርስቲያናት ከአንድ ቋጥኝ ተፈልፍለው የተዘጋጁ ናቸው። ሰቀልማ የሚባለው እንደ ጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ ያሉ አብያተክርስቲያናት ናቸው ።
[ለማስተካከል] ታቦት
[ለማስተካከል] ሕገ ኦሪት
[ለማስተካከል] የውጭ መያያዣዎች እና ዋቢ መጻሕፍት
- ይፋዊ EOTC ድረ-ገፅ (እንግሊዝኛና አማርኛ)
- የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሉሌ መልአኩ፤ ሦስተኛ እትም - ፲፱፻፹፮ ዓ.ም.

