መንግስቱ ኃይለ ማርያም

ከውክፔዲያ
መንግሥቱ ኀይለማሪያም
አምባገነን ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያዊ
ከግንቦት ፳ ቀን 1966 ዓ.ም. እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን 1983 ዓ.ም.
ጠቅላይ ሚኒስትር ተስፋዬ ዲንካ
ታምራት ላይኔ
ተከታይ ተስፋዬ ገብረ ኪዳን (ተግባራዊ)
የተወለዱት በግንቦት 27 በ1929 እ.ኤ.አ.
አዲስ አበባመንግሥተ ኢትዮጵያ
የፖለቲካ ፓርቲ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ
ይህን ታሪክ የጸፍው ግለሰብ የመንግስት ሀይለማሪያ ቀንደኛ ደጋፊ እንደሆነ ከፁሁፉ አንጸር መርዳት አያዳግትም ትክክለኛውን ታሪክ ከምንጭ ጋር እንደሚያስተካክልው ተስፍ አደርጋለሁ።

መንግሥቱ ኀይለማሪያምግንቦት 271929 እ.ኤ.አ.አዲስ አበባ ተወለዱ። አባታቸው ሃምሳዓለቃ ሃይለማሪአም ወልዴ፣ እናታቸው ብዙነሽ ተሰማ ነበሩ የአሁኑ መንግስት እና ብዙ የምእራባውያን መንግስታት እሱን እንደ ኮሚኒስት ተኮር አምባገነን አድርገው የሚቆጥሩት ሲሆን የቀድሞው አምባገነን ሮበርት ሙጋቤ የጥገኝነት ጥያቄውን ከተቀበሉ ወዲህ ወደዚምባብዌ ተሰዷል ፡፡ መንጌ በሀይማኖት በኩል ብዙ አጥፍቷል ኦርቶዶክስን ማዳከም የጀመረዉ በሱ የሰልጣን ግዜ ነወ የማይካድ ግን አገርወዳድ መሪ ነበር ማንም ባለሰልጣን ሰራገበተዉ ላይ የሚገኝ በዩኒፎርም ልብሰ ነበር ሌባ የለም ብቻ አገርወዳድ መሪ ነበር


ምንም እንኳን መንግስት እንደዚህ ያሉ ክሶችን በተደጋጋሚ ቢክድም በ 2006 (2008) በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ፍ / ቤት በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሷል ፡፡ ሆኖም በሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል እንዲከሰስ በሄግ አልተከሰሰም ፡፡

መንግስቱ ኃይለ ማርያም 1978

ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም' ከ1966 እስከ 1983 ዓ.ም. (1974 እስከ 1991 እ.ኤ.አ.) ለ17 ዓመታት የኢትዮጵያ መሪ ነበሩ። ወደ ስልጣን የወጡት በደርግ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን በመገልበጥ ሲሆን የአብዮቱ መሪ ሆነው ከቆዩ በኋላ በመለስ ዜናዊ በሚመራው በኢሓዴግ ሽምቅ ተዋጊ ቡድን እና በአሜሪካው የቀድሞው የሲአይኤ ዳሪክተር ሃርማንኮህ እርዳታ በ1983ዓ.ም ከስልጣን ተወገዱ። በአሁኑ የሀገሩ መንግስት እና በአብዛኞቹ የምዕራባውያን አገራት የኮሚኒስት አምባገነን ተደርጎ ፣

 ይህ መፈንቅለመንግስት በሲአይኤ ስውር ዘዴ የተከናወነ ሲሆን የህወሓትና የሻእብያው መሪ ከሱዳን በቦይን 777 ከቀድሞው ከሲአይኤ ዳሪክተር ከ ሃርማንኮህ ጋር ታጅበው አዲስ አበባ ገብተዋል።   ይህነው የኮሎኔል መንግሰቱ ኃይለማርያም የመንግሰቱ ግልበጣ ሳቦታጅ!! መንግስቱ ኃይለማርያም ያላሰበው ግልበጣ ተቀናብሮበት ያለአማራጭ በአየርላይ ቀረ እንጂ በራሱ ፍላጎት ሸሽቶ ዚምቡዋቤ ተሸሸገ የሚለው አባባል ከእውነት የራቀነው።   ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም በቃላቸው የሚገኙ አገር ወዳድ ጀግና ሰው እንደነበሩ እናውቃለን።

መንግሥቱ ኃይለማሪያም ወደ ርዕሰ ብሄርነት ሥልጣን ብቅ ሲሉ ገና የ፫፯ ዓመት ወጣት የነበሩ ሲሆኑ በሀረር የ3ኛ ክፍለ ጦር የመሳሪያ ግምጃ ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር። በወቅቱ በክፍለ ጦሩ አዛዥ የነበሩት ጀነራል ሓይሌ ባይከዳኝ የሚባሉ ኮ/ መንግስቱን በባህሪያቸው በመጠርጠራቸው ከአጠገባቸው ዞር ለማድረግ ወደ ኦጋዲን አዛውረዋቸው እንደ ነበር ይነገራል። በእዚያም ጥቂት ጊዜ በኋላ ለትምህርት ወደ አሚሪካ ሜሪላንድ ለወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት ተላኩ። ከትምህርት ሲመለሱም በ3ኛ ክፍለ ጦር የመሳሪያ ግምጃ ቤት ሃላፊ ሆነው ተሾሙ። ከዛም በደረጃ እድገት ካገኙ በሁዋላ የአፄ ኃይለስላሴን ጨቋኝ አገዛዝ ለመገርሰስ የደርግ ኩዴታን መሰረቱ በመኮንኖች ህብረት የተመሰረተው ደርግ በአብዛኛው ተደማጭነትና የፓለቲካ ብስለት በነበራቸው በቆራጥነታቸው ታዋቂ በሆኑት በመንግስቱ ኃይለማርያም ስልታዊ አደረጃጀት ተቀናብሮ የንጉሱን ወንበር ገለበጡት ይህ በሆነ ወቅት በነበረው አለመረጋጋት በከተማው የተኩስ ልውውጥ ተደረጎነበር። የመጀመርያውን ስልጣን በመያዝ የደርግ ሊቀመንበር ሆነው የተሾሙት ጀኔራል አማን አምዶም ነበሩ።

  በተለያየ አመታት በተለያየ ክህደትና አሻጥር የተገኙ አመራሮች ከስልጣን ሲወገዱ ቆይተው በአራ0ተኛው ዙር ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የኢትዮጵያ የመጀመርያው ፕሬዚዳንት ለመሆን በቅተዋል። 
የመንግስቱ ተቃዋሚዎች

ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት ሶማሊያየዚያድባሬ መንግስት በሶቭየቶች ተደግፋ ሀገራችንን ድንገት ወረረች። በወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩትን ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተርን ፈጣን ወታደራዊ እርዳታ ጠይቀው እሳቸውም የንጉሱ የቅርብ ወዳጅ ስለነበሩ በስዊስ ባንክ ያለውን የኢትዮጵያ ሃብት ለመንግስቱ ኃይለማርያም ከሰለመስጠት በተደረገው ውይይት የአሜሪካ እጅ ስለነበረበት መንግስቱ ነጮችን በ73 ሰአት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ አድርጎ ስለነበር በዚህ ቂም ጥያቄውን ሳይቀበሉ ቀሩ። በእዚህም ምክንያት አማራጭ ያጣው ደርግና መንግሥቱ ሀገሪቱ በከፍተኛ ስጋት ላይ በመውደቋ የግድ ወደ ሞስኮ መሳሪያ ልመና ልኡካን ላኩ። በሌላ በኩል ሞስኮ ከሶማሊያ ጋር ጥቅምዋን በማወዳደር ለመንግስቱ መሳሪያ መስጠት ካስፈለገ በፊርማ ሶሻሊስት ካምፐ መግባቱን እንዲያረጋግጡ ስለ ጠየቀች ኮ/መንግሥቱ ይህን በማድረጋቸው በይፋ የሚመሩት አብዩት የሌኒኒስት ማርክሲስት መሆኑን በአዋጅ አሳወቁ። ኮ/መንግሥቱ የቼጉቬራና የሶቬቱን ማርክሲዝም አሜሪካ ለወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት በተላኩበት ዘመን ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ሃር ሳይመለሱ ወደ ሞስኮ በማምራት የራሻን ሶሻሊዝም በግላቸው ተምረው ነበር፣ወደ አገር ሲመለሱም ንጉሱ በዚህ ድርጊታቸው ለሁለት አመት በኦጋዴን በረሃ በቅጣት እንዲቆዩ ተደርጎነበር። የመንግስቱ ስለሶቪየት ሶሸሰሊዝም ፖለቲካ እውቀት የሚያውቁት የቅርብ መኮንኖች በደርግ ኩዴታው የነቃውንና ብስለት ያለውን ደፋሩን መንግስቱ ኃይለማረወያምን ነበር በአደራጅነት የመደቡት። ከስምምነቱም በሁዋላ በ፪ ወር ጊዜ ውስጥ የብዙ ሚሊዮን ዶላር ታንክና የጦር መሣሪያ እርዳታ ማግኘት ብቻ ሳይሆን በሞስኮ በኩል የኩባን የጦር አማካሪዎች በማግኘታቸው የወራሪውን የሶማሊያን ኃይል መመከት ችለዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አሜሪካ የጭንቅ ጊዜ ጥያቄ መላሽ ሆና ባለመገኘትዋና በንጉሱ ስም በስዊስ ባንክ የተቀመጠውን በትሪሊዮን የሚቆጠር ዶላርና ወርቅ የስዊስ ባንክ ለኢትዮጵያ መንግስት እንድትመልስ መንግስቱ ኃይለማረወያም ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ በማድረጓ የአሜሪካ ትብብር በመኖሩ ምክንያት መንግስቱ ኃይለማርያም በስልጣን እስከቆዩበት ዘመን ሁሉ በዋና ጠላትነት ተፈርጀዋል። አንዳንድ ሚሲዮናዊያንንም ከአገር አባረሩ። በንጉስ ኃይለስላሴ ፊርማ በስዊስባንክ የነበረው የኢትዮጵያ ሃብት እስካሁን አልተመለሰም። አብይ አህመድ ይህን የመጠየቅ ወኔ የለውም፣ምፅዋእት ከመለመን በቀር።

በወቅቱ በአገር ውስጥ ግንባር ቀደም ተቃናቃኝና ተቃዋሚ ከነበረው ከኢህአፓ ጋር የከተማ ለከተማ ውጊያና መገዳደል ተጀመረ። ሁለቱም ወገኖች ቀን በቀን ግድያም ለብዙ ወጣትና አዋቂ እልቂት ምክንያት ሆኑ። 

መንግሥቱ ኃ/ማሪያም በወታደራዊ አመራር ውስጥ የተከስተው የስልጣን ዝቀጠትና ምግባረ ብልሹነት፤ የደህንነቱ ክፍል በሁለት ቢላዋ መብላት፣ ተደማምሮ ውድቀታቸውን እንዳፋጠነው የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። የመንግስቱን አስተዳደር ለውድቀት ያበቃው የኮሎኔሉ አምባገነን አመራር ነው የሚሉት ተቀናቃኞቻቸውና በሁለት ቢለዋ እየበሉ አገርን ለመሸጥ ያስማሙ የነበሩ በወቅቱ (በመኢሶን) ውስጥ ተሰግስገው የነበሩ የኦነግ ስውር ባንዳ መኮንኖችና የ(TPLF) እና የ (EPLF) ሰላዮችና አገር በሆድና በስልጣን የሸጡ የመንግስቱ ተቀናቃኞች መረጃን አሾልኮ ለተቃዋሚ ኃይሎች አሳክፎ በመስጠት እንደሆነ ይታወቃል። በመንግስቱ ኃይለማርያምላይ የተቀነባበረ የ 16 ግዜ የመግደል ሙከራ ተደርጎባቸው አምልጠዋል። ጠላቶቻቸው ከውስጥና ከውጭ ብዙ ስለነበሩ ለ17 አመታት ቀንና ሌሊት ሲዋጉ አገርን በልማት በምርት ዘመቻ፣በትምህርትዘመቻ፣እንዲሁም ስራአጥነትንና ሴተኛ አዳሪነትን ለማስወገድ የኢንዱስትሪ ስራዎችን በመክፈትና በማስፋፋት መሬትን ለአራሹ በመሰከፋፈል፣ ለደሃው ህዝብ ርካሽ የቤትክራይን በመደንገግ፣ለአገራቸው ከፍተኛ አገልግሎት ያበረከቱ ታላቅ መሪናቸው። ይህን በጎ ተግባራቸውን ለመናገር የሚያንቃቸው የግል ጥቅማቸውን ከአገር ጥቅም ይልቅ አብልጠው የሚወዱ ተቀናቃኝ ሰዎች ብቻ ናቸው። መንግሥቱ (የቀድሞው) ርዕሰ ብሔር ማንኛውም መሪ ላይ ሊከሰት የሚችል ስህተት ነው የፈፀሙት...ስለ ሐገር ስለ ብሔራዊ ክብር እና ኩራት ግን እርሳቸው ! ከፊት ቢሠለፉ የሚገባቸውና የሚያምርባቸው ናቸው።

የኮሎኔል መንግስቱን ህይወት ተቀጥፋ ለማየት የጓጉና የፎከሩ ሁሉ ቀድመዋቸው ሞተዋል!!
   የእድሜ በለፀጋው ጓድ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሦስት ልጆች አባት ሲሆኑ 3ስቱም ልጆቻቸው ዶክተሮች ናቸው። ዛሬ የ 83 አመት አዛውንት ሆነው በሃራሬ በህይወት ይገኛሉ። 

[1][2]

ማህበራዊ አውታረ መረቦች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማጣቀሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ http://www.madote.com/2018/08/why-photo-of-mengistu-haile-mariam-has.html
  2. ^ https://borkena.com/2018/08/01/hailemariam-desalenge-met-colonel-mengistu-hailemariam-in-zimbabwe/