Jump to content

አባላ አባያ

ከውክፔዲያ
አባላ አባያ
Abbala Abbaayaa
ወረዳ
በአባላ አባያ አባያ ሀይቅ ዳርቻ
ሀገር ኢትዮጵያ
ክልል ደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት
ዞን ዎላይታ
ርዕሰ ከተማ አባላ ፓራቾ
የሕዝብ ብዛት
   • አጠቃላይ 56,812

አባላ አባያ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በዎላይታ የሚገኝ ወረዳ ነው። ወረዳው 16 የቀበሌ አስተዳደሮችን ያቀፈ ሲሆን ከነዚህም 13ቱ ገጠር 3ቱ ደግሞ ከተማ ናቸው። በ6°38′ N ኬክሮስ እና 37° 42′ E ኬንትሮስ መካከል ተቀምጦ ከአዲስ አበባ በደቡብ 419 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል። ወረዳው የተቋቋመው እኤአ በ2019 ከአካባቢው ወረዳዎች ነው። [1] አባላ አባያ በደቡብ በኩል በአባያ ሀይቅ[2] በምዕራብ በሁምቦ ወረዳ፣ በሰሜን በሶዶ ዙሪያ ወረዳ፣ በምስራቅ በሆቢቻ ወረዳ ይዋሰናል። የዚህ ወረዳ የአስተዳደር ማዕከል አባላ ፓራቾ ከተማ ነው።

የህዝብ ብዛት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የዚህ ወረዳ አጠቃላይ ህዝብ 56,812 አካባቢ ነው። ከዚህም በወረዳው 27,627 አባወራዎች ያሉ ሲሆኑ ከነዚህም 16,981 ወንድ እና 10,646 ሴት አባወራዎች ናቸው። [3]

ዋቢ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "Abala Abaya woreda". Archived from the original on 2023-06-10. በ2024-06-23 የተወሰደ.
  2. ^ "direction to Abala Abaya district". Archived from the original on 2021-09-08. በ2024-06-23 የተወሰደ.
  3. ^ "Assessing climate change-induced poverty of mixed crop-livestock smallholders in Wolaita zone". Research in Globalization (ScienceDirect) 7. https://www.sciencedirect.com/science/article/pii/S2590051X23000485.