ኬብሮን

ከውክፔዲያ
በኬብሮን ውስጥ አብርሃም ከኬጢያዊው ከኤፍሮን የገዛው የመቃብር ዋሻ ስፍራ፥ ከሕንፃ በታች ሲታይ

ኬብሮን በምእራብ ባንክ ውስጥ በጣም ጥንታዊ ከተማ ነች። አሁንም 250,000 ነዋሪዎች አሏት። አብዛኞቹ [የፍልስጤም አረቦች] ናቸው እነሱም አሉ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ኬብሮን አብርሃም መቀመጫ ናት በክርስትናም ሆነ በእስልምና እንደ ቅዱስ ቦታ ተወስዷል።

ኦሪት ዘኊልቊ 13፡22 በከነዓን ዘምተው የእስራኤላውያን አርበኞች ወደ ኬብሮን በደረሱ ጊዜ፥ «በግብፅ ካለችው ከጣኔዎስ በፊት ስባት ዓመት ተሠርታ» የሚለውን መጠሪያ እንዳገኘ ይገለጻል። ይህ መረጃ ደግሞ ከመጽሐፈ ኩፋሌ 11:23 ሊገኝ ይችላል። አብርሃም ወደ ግብጽ በሄደበት ዘመን፥ «የግብጽ ክፍል የምትሆን ጣይናስም ያን ጊዜ ከኬብሮን በኋላ በሰባት ዓመት ተሠራች።» በዚህ አከፋፈል ኬብሮን የተሠራች በ1954 ዓ.ዓ. (2117 ዓክልበ. ግድም) ሆነ።