Jump to content

ክርስቶስ

ከውክፔዲያ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ

መኑ ውእቱ ሐሳዊ ዘእንበለ ዘይክሕድ ወይብል ከመኢየሱስ ኢኮነ መሢሐ---ኢየሱስ መሢሕ አይደለም ከሚል በቀር(የሚል ነው እንጅ) ሐሰተኛ ማን አለ???[1]

ሃይማኖት መሢሐዊት ክፍል አንድ---ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆኑት መምህር በትረማርያም አበባው የሚሏቸው ሊቅ

“ድርሳነ ቄርሎስ ላይ የተጠየቁ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው ክፍል ፮”

በሚል ርእስ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ የጻፉት መልእክት ነው፡፡ መምህሩ ሲጀምሩ

“ድር.ቄር.40፥8 እግዚአብሔር አምላክህ የደስታ ዘይትን ቀባህ እንደ አንተ ካሉት ይልቅ ሲል እንደ አንተ ካሉ የተባሉት እነ ማን ናቸው?” ብለው ይጠይቁና ለዚህ ምላሽ ይሆናቸው ዘንድ “[2]

“መልስ፦ ይህ ስለክርስቶስ የተነገረ ነው። ሥጋ በተዋሕዶ አምላክ ሆኗል። ሥጋ አምላክ ይሆን ዘንድ የቀባው (ያከበረው) ማን ነው? ከተባለ ደግሞ በማክበር ሦስቱ አንድ ስለሆኑ ለአብም፣ ለወልድም፣ ለመንፈስ ቅዱስም ይነገራል። የደስታ ዘይት የተባለ መንፈስ ቅዱስ (አምላካዊ ክብር) ነው። ሀብተ መንፈስ ቅዱስን የሚያመለክት እንደሆነ የሚገልጽልን እንደአንተ ካሉት ከተባሉት ከነቢያት የበለጠ ተብሎ በመገለጹ ነው። እንደ አንተ ያሉት የተባሉት ነቢያት፣ ቅዱሳን፣ በጠቅላላው የጸጋ ልጅነትን ገንዘብ ያደረጉ ናቸው። የደስታ ዘይት የተባለ አካለ መንፈስ ቅዱስ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። አካለ መንፈስ ቅዱስ በሁሉ የመላ ስለሆነ ከአንዱ የሚጎድል ከአንዱ የሚበዛ አይደለምና። ነቢያት ጸጋውን፣ ሀብቱን ገንዘብ አድርገዋል እንጂ አካሉን ገንዘብ አድርገዋል አልተባለምና። ስለዚህ ክርስቶስ ከነቢያት የሚበልጥ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ አደረገ መባሉ የነቢያት ክብር የጸጋ፣ የእርሱ ክብር ግን የባሕርይ መሆኑን ያመለክታል። የደስታ ዘይት የተባለ አምላካዊ የባሕርይ ክብሩ እንደሆነ ያመለክታል”

በማለት ራሳቸውንና የዋሁን የሀገሬን ትውልድ በደረቁ ሲላጩት ይገኛሉ፡፡ ምሥጢረ ተቀብዐ አያሌ ሊቃውንትን ሲፈትናቸው ሲፈታተናቸው የሚታይ ነው፡፡ በቅርቡ እንኳን ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን “ቅቡዕ” የሚለውን ቃል አይተው ዕ እስከምታንቃቸው ድረስ ሲንደፋደፉበትና ሲጨነቁበት ያየነው የአደባባይ ሐቅ ነው፡፡ ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ “ተቀብዐ” የሚል አንቀጽ ሲያገኙ ስለሚያቃዣቸው “ተለዐለ” ወይም ደግሞ “ተሰብአ”፤ እንደዚህም አልመቻቸው ሲል ባላየ በማለፍ ተክነውበት ይገኛል፡፡ በአማን ነጸረ የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስን እየለወጡ የመተርጎምና የባላየ አካሄድን “ምሥጢሩን እየተከተለ ተለዋጭ ግሶችን መተካት” በሚል ራሳቸውን ሲያታልሉና ክሕደታቸውን በማይገናኝ ምሥጢር ሲሸውዱ ይገኛሉ፡፡ ሌሎች አብነቶችን ብንመለከት ኢትዮጵያውያ የተቀብዐ ጸዋምያን ብዙ ይላሉ፡፡ ጉዳዩ ግን በዚህ ልክ የሚያታልሉትና የሚሸውዱት መሢሑን ነውን?ወይስ ራሳቸውን?ወይስ ደግሞ ምእመናንን?ማንን ነው በዚህ ልክ የሚሸውዱት ብለን እንጠይቅ ዘንድ እንገደዳለን፡፡

እኔ ግን እላለሁ ተቀብዐን ለውጦ መተርጎም፣ አንጻሩን አስለቅቆ በዚህ ልክ መግቢያ መውጫ ማጣት መሲሑን መካድ ነውና ሐሳዊ መሆን ነው እላለሁ፡፡ በተጨማሪም “ወስሞሰ ለክርስቶስ ኢየአምሩ ወዘኢይደሉ ይሜህሩ----የክርስቶስን ስም አላወቁምና የማይገባውን ያስተምራሉ” በሚለው የሊቁ ዘለፋ እዘልፋቸው ዘንድ እወዳለሁ፡፡

ተቀብዐ ከሌለ ክርስቶስ ማለት የለም ፤ ክርስቶስ ማለት ከሌለ ክርስትና ማለት የለም እርምና እንጅ፡፡ ስለሆነም የዚህ ጽሁፍ አንባብያን ወገኖቻችን ሆይ ነገሩን ሁልጊዜ በተቃዋሚነት አልያም ደግሞ በአልቀበልም ባይነት ሳትመለከቱት መሬት ላይ ያለው ነባራዊ ሐቅ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት የተናገሩት እውነት ምንድን ነው የሚለውን መርምረን እንመለከት ዘንድ መልእክቴ ነው፡፡

ዐምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ እግዚአብሔር ወልድ ሰው በመሆኑ በቅብዐተ መንፈስ ቅዱስ መክበሩንና በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ በመክበሩም ክርስቶስ እንደተባለ ቁልጭ አድርጎ አስተምሯል፡፡ መሢሕነቱን እናምናለን የሚሉቱ እነ መምህር በትረ ማርያም ግን የሊቁን ቃል ወደራሳቸው አረዳድ እየጠመዘዙ የመድኃኒታችንን መሢሕነት ሙልጭ አድርገው ክደውት ይገኛሉ፡፡

ቅዱስ ቄርሎስ ክቡር ዳዊት “በትረ ጽድቅ ወበትረ መንግሥትከ፤ አፍቀርከ ጽድቀ ወአመፃ ጸላዕከ፤ በእንተዝ ቀብዐከ እግዚአብሔር አምላክከ ቅብዐ ትፍሥሕት እምእለ ከማከ--ጽድቅን ወደድክ አመፃንም ጠላህ፤ ስለዚህ፤ እግዚአብሔር አምላክህ ከባለንጀሮችህ ይልቅ(የሚበልጥ) የደስታ ዘይትን ቀባህ” ብሎ በመዝሙር 44 ላይ የተናገረውን ቃል ሲተረጉምልን፤-

“ያአምን ክቡር ዳዊት---ክቡር ዳዊት ያምናል፡፡ አንድም ወልድ ሰው ሁኖ በሰውነቱ በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ እንደከበረ ያምናል ያሳምናል፡፡ እንዘ ይብል በእንተ ወልድ መንበርከ አምላኪየ ለዓለም ዓለም---አምላኬ ሆይ ዙፋንህ ለዘለዓለም ነው ብሎ፡ አንድም በማለት ያአምን፡፡ በትረ ጽድቅ ወበትረ መንግሥትከ---አንድ ወገን ነው የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው፡፡ አፍቀርከ ጽድቀ ወአመፃ ጸላእከ---ጽድቅን ወደድክ አመጻንም ጠላህ፡፡ በእንተዝ---ስለዚህም፡፡ ቀብዐከ እግዚአብሔር አምላክከ ቅብዐትፍሥሕት እምእለከማከ--እግዚአብሔር አምላክህ ከባለንጀሮችህ ይልቅ የደስታ ዘይትን ቀባህ ብሎ ፤ አንድም እንዲህ በማለቱ፤ አንድም ይህንን በመናገሩ እንደከበረ ያምናል ያሳምናል ያስረዳል” በማለት የክቡር ዳዊትን እምነትና የወልድን በሰውነቱ በቅብዐተ መንፈስ ቅዱስ መቀባቱን ይገልጣል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ይቀጥልና “ለቡኬ ከመ አምላክ ሰመዮ---እንደ አምላክ ሰም አውጥቶለት ማለት አምላክ ብሎት(አምላኪየ ብሎታልና) አንድም አምላክ ካለው በኋላ፤ ወመንበረሂ ውሂቦ ዘለዓለም---የዘለዓለም መንበርም ሰጥቶት ማለት መንበርም ሰጥቶ ሳለ(መንበረከ እግዚኦ ለዓለም ዓለም ብሎታልና) አንድም የዘለዓለም ዙፋን ገንዘቡ እንደሆነ ተናግሮ አንድም ከተናገረ በኋላ፤  ሰመዮ ከመ ተቀብዐ እምእግዚአብሔር---ከእግዚአብሔር በተገኘ ቅብዐት እንደተቀባ ጠራው ማለት ከእግዚአብሔር በተገኘ ክብር እንደከበረ ተናገረ አንድም ከእግዚአብሔር በተገኘ ክብር ከበረ እንዳለው አስተውል ፤ ዘውእቱ ገሀደ እምእግዚአብሔር አብ---ይኸውም(እግዚአብሔር አምላክህ ቀባህ ማለቱም) በጎላ በተረዳ ነገር ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር አብ የተገኘው ክብርም አካለ መንፈስ ቅዱስ ነው(ቅብዐ ትፍሥሕት) አንድም ዘውእቱ ይኸውም ከአብ የተገኘ አካላዊ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ በቅብዐተ ነከራ እምእለ ተሳተፎሙ ንሕነ---እም እለተሳተፎሙ (እምእለከማከ ያለውን ሲያጎላው ነውና ጆሮ ያለው ይስማ) የተባልን እኛ ነን እኛ ካገኘነው ክብር በሚበልጥ ክብር ከበረ እንዳለው እወቅ፡፡ አንድም በነፍስ በሥጋ የመሰለን እኛ ከከበርንበት ልዩ ድንቅ በሚሆን ከእግዚአብሔር አብ በተገኘ ክብር ከበረ እንዳለው እወቅ፡፡ እመኒ ኮነ ሰብአ በአማን እግዚአብሔር ቃል ውእቱ---ምንም ሰው ቢሆን እግዚአብሔር ነው”


ክርስቶስ ማለት ከግሪክኛ ቋንቋ Χριστός ነው፤ ይህም ለመሢሕ (ከዕብራይስጥ ማሺያሕ ወይም «የተቀባ») ትርጒም ነው። በክርስትና እምነት እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ (ረቢ ይሆሹዓ) ስያሜ ይጠቀማል፤ «የተቀባ» ማለትም ወልድ (ከሥላሴ አንዱ) ሆኖ ለንጉሥነት ማለት ነው። «በእርሱ የመለከት ሙላት ሁሉ በሰውነት ተገልጦ ይኖራልና» (ቈላስ. ፪፣፱) በአዲስ ኪዳን የተመሠረተ እምነት ነው። በትምህርተ ሥላሴ ዘንድ እሱ ብቻ መላው አምላክ ሳይሆን የፈጣሪው ክንድ ወይም አካል ነው፤ እንደ አብመንፈስ ቅዱስ ሆኖ ደግሞ በሌሎች ቦታዎች አለ።

ብሉይ ኪዳን ደግሞ “መሲሕ” مسيح የሚለው የአረቢኛ ቃል “መሢሐ” מָשִׁ֫יחַ የሚለው የእብራይስጥ ቃል “መሢሕ” ክמשיחא የሚለው የአረማይ ቃል ሴማዊ መነሻ ሲኖረው ትርጉሙ “የተቀባ” ማለት ነው፣ በግሪክ ደግሞ “ክርስቶስ” Χριστός ነው፤ ይህ ማእረግ በብሉይ ኪዳን ለተለያየ ነገስታትና ነቢያት በግሪኩ ሰፕቱጀንት ላይ “ክርስቶስ” Χριστός በእብራይስጡ ደግሞ መሢሐ” מָשִׁ֫יחַ ተብሎ አገልግሎት ላይ ውሏል፤ መቀባት መሾምን ያመለክታል በአምላክ የተቀቡ የአምላክ መሢሖች ብዙ ናቸው፦ 1ኛ ዜና 16፥22 “መሢሖቼን” בִּמְשִׁיחָ֔י አትዳስሱ፥ “በነቢያቴም” ክፉ አታድርጉ ብሎ፥ ሰው ግፍ ያደርግባቸው ዘንድ አልፈቀደም ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ። መዝሙረ ዳዊት 105፥14-15 “መሢሖቼን” בִּמְשִׁיחָ֔י አትዳስሱ፥ “በነቢያቴም” ክፉ አታድርጉ ብሎ፥ ሰው ግፍ ያደርግባቸው ዘንድ አልፈቀደም ስለ እነርሱም ነገሥታትን ገሠጸ።

አንደኛ “ሳኦል” 1ሳኦል በትንቢት የተነገረለት መሢሐዊ ንጉስ ነው፦ 1 ሳሙ 2:10 እግዚአብሔር እስከ ምድር ዳርቻ ይፈርዳል፤ “ለንጉሡም” ኃይል ይሰጣል፤ “የመሲሑንም” מְשִׁיחֽוֹ ቀንድ ከፍ ከፍ ያደርጋል።

ይህንን ጥቅስ የአይሁድ ምሁራን እና ለዘብተኛ የብሉይ ተንታኞች ለሳኦል እንደሆነ ያትታሉ፤ በተጨማሪም በሳሙኤል ዘመን የተቀባ መሢሕ ሳኦል እንደሆነ በቁና መረጃ አለ፦ 1ሳሙ 10:1፤ ሳሙኤልም የዘይቱን ብርሌ ወስዶ በራሱ ላይ አፈሰሰው፥ ሳመውም፥ እንዲህም አለው። በርስቱ ላይ አለቃ ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር “ቀብቶሃል” מְשָׁחֲךָ ֧፤ 1ሳሙ 12፥3 እነሆኝ በእግዚአብሔርና “በመሲሑ” מְשִׁיח֗וֹ ፊት መስክሩብኝ የማንን በሬ ወሰድሁ? 1ሳሙ 12፥5 እርሱም፦ በእጄ ምንም እንዳላገኛችሁ እግዚአብሔርና “መሲሑ” מְשִׁיח֗וֹ ዛሬ በእናንተ ላይ ምስክሮች ናቸው አላቸው፤

ሁለተኛ “ዳዊት” 2 ሳሙ 22፥51 የንጉሡን መድኃኒት ታላቅ ያደርጋል፤ ቸርነቱንም ለመሲሑ לִמְשִׁיח֛וֹ ለዳዊትና ለዘሩ፥ ለዘላለም ይሰጣል። 2 ሳሙ 23፥1 የዳዊትም የመጨረሻ ቃሉ ይህ ነው። ከፍ ከፍ የተደረገው፥ የያዕቆብም አምላክ መሢሕ מְשִׁ֙יחַ֙፥ በእስራኤል ዘንድ መልካም ባለ ቅኔ የሆነ፥ የእሴይ ልጅ የዳዊት ንግግር፤ መዝ 132:17 በዚያ ለዳዊት ቀንድን አበቅላለሁ፥ “ለመሢሔ” לִמְשִׁיחִֽי ሰው መብራትን አዘጋጃለሁ።

ሶስተኛ “ሰለሞን” 1ሳሙ 2:35 የታመነም ካህን ለእኔ አስነሣለሁ፥ በልቤም፥ በነፍሴም እንዳለ እንዲሁ ያደርጋል፤ እኔም የታመነ ቤት እሠራለታለሁ፥ ዘመኑን ሁሉ በመሢሔ מְשִׁיחִ֖י ሰው ፊት ይሄዳል።

ይህ ጥቅስ ትንቢት ሲሆን ትንቢቱም ስለ ካህንና ካህኑ የሚሄድበት መሢሑ ናቸው፤ ምሁራን ካህኑ ሳዶቅ ሲሆን መሢሑ ደግሞ ቤት የሰራው ሰለሞን ነው፦ 1 ኛ ነገሥት 1፥39 ካህኑም ሳዶቅ ከድንኳኑ የቅብዓቱን ቀንድ ወስዶ ሰሎሞንን ቀባ וַיִּמְשַׁ֖ח፤ ቀንደ መለከትም ነፉ፤ ሕዝቡም ሁሉ፦ ሰሎሞን ሺህ ዓመት ይንገሥ አሉ።

አራተኛ “ሴዴቂያስ” ምሁራን በባቢሎን ምርኮ ጊዜ በጉድጓድ የተያዘው ሴዴቅያስ እንደሆነ ያትታሉ፤ ይህም ንጉስ መሲህ ተብሏል፦ ሰቆእንኖራለንቃው ኤርምያስ 4፥20 ሬስ። ስለ እርሱ። በአሕዛብ መካከል በጥላው በሕይወት ያልነው “የእግዚአብሔር መሢሕ” מְשִׁ֣יחַ፥ የሕይወታችን እስትንፋስ፥ በጕድጓዳቸው ተያዘ።

አምስተኛ “ሙሴና ኤልያስ” ዘካ 4:14 እርሱም። በምድር ሁሉ ጌታ አጠገብ የቆሙት “ሁለቱ የተቀቡት” הַיִּצְהָ֑ר እነዚህ ናቸው አለኝ።

በምድር ሁሉ ጌታ አጠገብ የቆሙት “ሁለቱ የተቀቡትየተባሉት ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን ካዘጋው ከኤልያስና ውኃዎችንም ወደ ደም ካስለወጠው ከሙሴ ሌላ እነማን ሊሆኑ ይችላሉ? ምሁራን በዚህ ሸክ የላቸውም፦ ራእይ 11፥3-10 “ለሁለቱም ምስክሮቼ” ማቅ ለብሰው ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን “ትንቢት” ሊናገሩ እሰጣለሁ። እነዚህ “በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ” ሁለቱ ወይራዎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው። ዘካርያስ 4፥11 እኔም መልሼ፦ በመቅረዙ በስተ ቀኝና በስተ ግራ ያሉ እነዚህ “ሁለት የወይራ ዛፎች” ምንድር ናቸው? አልሁት። ዘካ 4:14 እርሱም። በምድር ሁሉ ጌታ አጠገብ የቆሙት “ሁለቱ የተቀቡት” הַיִּצְהָ֑ר እነዚህ ናቸው አለኝ።

ስድስተኛ “ኢየሱስ” መዝሙረ ዳዊት 2፥2 የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ מְשִׁיחֽוֹ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ።

ክርስቶስ ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከባሕርይ አባቱ ከአብ ፣ ድኀረ ዓለም ያለ አባት ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ የተወለደ፣ ሥጋን እና ነፍስን ከቅድስት ድንግል ማርያም ነሥቶ ሰው የሆነ የባሕርይ አምላክ ነው::የሰውን ልጅ ከባርነት ነጻ ለማውጣት ፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከባርነት ወደ ነጻነት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን ለማሸጋገር፤ ፍቅር ከዙፋኑ ስቦት የወረደ፤ አምላክ ነው ኢየሱስ ክርስቶስ::

ክርስቶስ ኢየሱስ ቸር እረኛ፣ አምላክ፣ ወልደ አምላክ፣ ሰውም አምላክም፣ ሲሆን በክርስቲያኖች መካከል ስለ ባሕርይው የተለያዩ አመለካከቶች አሉ::በጥንታዊት ቤተክርስቲያን ማለትም ከጉባኤ ኬልቄዶን በፊት አንዲት ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን በነበረችበት ወቅት ያለው አስተምህሮ 'ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው ፤አምላክ ነው፤ አምላክ ደግሞ አንድ ባሕርይ አለው፤ ክርስቶስም አንድ ባህርይ አንድ አካል አለው ይል ነበር:: ከሁለት አካል አንድ አካል፣ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ፣ ሰውም አምላክም፣ ትስእብት(ሥጋ) ከመለኮት ጋር ፍጹም ከተዋሐደ በኋላ እንደ ሁለት አካል ወይም ባህርይ አይቆጠርም ፤ብላ ታስተምር የነበረች አለማቀፋዊት ቤተክርስቲያን በጉባዔ ኬልቄዶን ከሁለት ተከፈለች::ይህም አንድ ባሕርይ እና ሁለት ባሕርይ በማለት ነበር::

ነገር ግን ማንም ክርስቲያን ቢሆን አሁን ላይ ያለው እምነት ክርስቶስ የዓለም መድህን፣ የእግዚአብሔር ልጅ ፣ የሕይወት መገኛ፣ ህብስተ ሕይወት፣ መንገድ እና መልካም እረኛ እንደሆነ፤ የሰውን ልጅ ድንቅ በሆነ ፍቅሩ ከሰይጣን አገዛዝ ነጻ ያወጣ ፣ በምድር አባት በሰማይ እናት የሌለው ፣ ሁለት ልደታት ያለው፣ ከብርሃን የተገኘ የዓለም ብርሃን ፣ ቅን ፈራጅ እና እውነተኛ ዳኛ እንደሆነ ይታመናል:: ክርስቶስ በክርስትና ዓለም ላሉ ሰወች መራራ ሞትን ሞቶ ሕይወትን የሰጠ ፣መራራ ከርቤን ጠጥቶ ጣፋጭ ወይንን(ደሙን) ያጠጣ፣ ራቁትን ሆኖ ፀጋን ያለበሰ፣ ተሰቅሎ ሰይጣንን ከፊታችን ጠርቆ ያስወገደ ፣ ተርቦ ሰማያዊ ሕብስትን ያበላ የሁሉም አዳኝ መሆኑ ይታመናል::

ክርስቶስ-«ሁሉም በእርሱ ሆነ፥ (በእርሱ ተፈጠረ)፥ ከሆነውም (ከተፈጠረውም) ሁሉ ያለ እርሱ ምንም የሆነ የለም። ዮሐ ፩፥፫።-ተብሎ እንደተጻፈ፤ ደግሞም በትንቢት ነብዩ ኢሳይያስ <<ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።>> ተብሎ እንደተተነበየ፤ በወንጌልም <<ቃል እግዚአብሔር ነበረ>> ተብሎ የምሥራች እንደተነገር፤ በዮሐንስ ወንጌል ሐዋርያው ቶማስ ጌታዬ አምላኬ ብሎ እንደመሰከረ፤ ክርስቶስ እግዚአብሔር መሆኑ በብዛት ባለንበት ዓለም ይታመናል::ነገር ግን ከዚህ የተለየ እምነት በአለማችን እንዳለም ይታወቃል::

:
  1. ድርሳነ ቄርሎስ
  2. @tedyazme