Jump to content
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መጋቢት 19
መጋቢት ፲፱
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የንግድ እና ኢንዱስትሪ ማዕከል እንዲሁም የቱርክ ርዕሰ ከተማ የሆነችው ‘አንጎራ’ ስሟ ተለውጦ አንካራ ስትባል፤ የአገሪቱ አንደኛ ከተማ እና በሮማይስጡ ቄሳር ቁስጥንጢኖስ የተመሠረተችው ቁስጥንጢንያ ወይም ኮንስታንቲኖፕል (Constantinople) ስሟን ቀይራ ኢስታንቡል ተባለች።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አብዮት ሲፈነዳ ከተሰነዘሩት ዐበያት ሕዝባዊ እሮሮዎች አንዱ በመሳፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ሚኒስትሮችና ባለሥልጣናት ግፈኝነት እና ሙስና ስለነበር ይሄንኑ ጉዳይ እንዲያጠና የተመሠረተው ኮሚሲዮን አባላት ተሠየሙ።
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በደቡብ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ፤ በጆሃንስበርግ ከተማ፣ በዙሉዎችና ‘የአፍሪቃ ብሔራዊ ሸንጎ’ (African National Congress) ደጋፊዎች መኻል በተከሰተው ሽብር አሥራ ስምንት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
-