ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መጋቢት 22
- ፲፱፻፳፰ ዓ.ም.፣ ኢትዮጵያ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አዝማችነት ከኢጣሊያን ሠራዊት ጋር በማይጨው ጦርነት ገጠመች
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት፣ የታኅሣሥ ግርግር መሪ የነበሩት ሜጀር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ በተሰቀሉ ማግሥት በተደረገው ሹም ሽር ጸሐፌ ትእዛዝ አክሊሉ ሀብተ ወልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙ፣ በጊዜው በሎንዶን አምባሳዶር የነበሩት ልጅ እንዳልካቸው መኮንን ደግሞ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስትር ሆነው ተሾሙ። ልጅ እንዳልካቸው የ ስድሳ ስድስቱ አብዮት ሲፈነዳ ጸሐፌ ትእዛዝ አክሊሉን በመተካት ከ ሠላሳ ሦስቱ ድል በኋላ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ሦስተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል። ሁለቱም ጠቅላይ ሚኒስቶች በዚሁ አብዮት ተገድለዋል።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ፓሪስ የመንገደኛ መሥመር፣ የመጀመሪያውን በረራ አከናወነ።