ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 5

ከውክፔዲያ

ታኅሣሥ ፭

  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ዓላማውን ይፋ አደረገ። አብሮም የለውጥ ፈላጊ ናቸው የሚባሉትን ልዑል ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መሾማቸውንና አልጋ ወራሹን አስፋ ወሰንን (“አስገድደው”) በማስማማትም መንግሥት በቆረጠላቸው ደመወዝ እየተዳደሩ ለሕገ መንግሥት የሚገዙ ንጉሥ ሆነው እንደሚያገለግሉ እራሳቸው ለሕዝቡ በራዲዮ እንዲያስተላልፉ አደረጉ።
  • ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - ዲክ ታይገር (ሪቻርድ ኢሄቱ) የሚባለው ናይጄሪያዊ ቦክሰኛ በተወለደ በ ፵፪ ዓመቱ በጉበት ነቀርሳ ምክንያት አረፈ። ዲክ ታይገር የባያፍራን የመገንጠል ሙከራ ደጋፊ ነው በሚል ወደአገሩ እንዳይመለስ ተከልክሎ በስደት አሜሪካ ይኖር ነበር።