ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ጥቅምት 9

ከውክፔዲያ

ጥቅምት ፱

  • ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የአሜሪካ መንግሥት ለፍንጫ ወንዝ ልማት የተመደበ ፸፭ ሚሊዮን ብር የብድር ውል ከኢትዮጵያ ንጉዛት ጋር ተፈራረመ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኅብረተ-ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት፣ የቀድሞ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት ባለሥልጣናት የሚዳኝ ወታደራዊ የፍትሕ ሸንጎ መሠረተ።
  • ፲፱፻፸፱ ዓ/ም - የሞዛምቢክን ፕሬዚደንት ሳሞራ ማሼልን እና አብረዋቸው የሚጓዙ ፴፫ ሰዎችን የጫነው አየር ዠበብ በአገሪቱ ውስጥ ሌቦምቦ ተራራ ጋር ሲጋጭ ተሳፋሪዎቹ ሕይወታቸው አልፏል።
  • ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴን በነፍሰ ገዳይነት እና በሰፊው በሰው ልጅ ላይ ወንጀል ሠርተዋል በመባል ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፣ ከተከሰሱባቸው ወንጀሎች ሁሉ ነፃ መሆናቸውን መሰከሩ።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - በከፍተኛ ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ የሚፈለጉ ኢትዮጵያውያንን በሞያሌ በኩል ሸኝተው ለማስኮብለል የሞከሩ የውጭ ዜጋ የሆኑ ሁለት የአውሮፓ ኮሚሽን ሠራተኞች በወንጀል ከተጠረጠሩት ኢትዮጵያውያን ጋር በዛሬው እለት እጅ ከፍንጅ ተያዙ ከተባለ በኋላ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ዋና መምሪያ ይህን ህገ ወጥ ተግባር የፈፀሙት ሁለቱ የውጪ ዜጎችም ከአገር እንዲወጡ መወሰኑን ገለፀ፡፡